🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ የካቲት 29/2018 (ኢዜአ)፦ በክህሎት፣ በእውቀትና በስነምግባር የታነፀ ትውልድ ለማፍራት የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የስራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገለፁ።
የኢፌዴሪ ቴክኒክና ሙያ ኢንስቲትዩት በቦሌ አራብሳ አካባቢ ያስገነባውን የቅድመ አንደኛ ትምህርት ቤት ምረቃ እና የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የግንባታ ማስጀመሪያ መርሀግብር አካሂዷል።

የስራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት፣ በክህሎት የዳበሩ ህፃናትና ታዳጊዎችን ለማፍራት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።
ዛሬ የተመረቀው የማህበረሰብ አቀፍ ትምህርት ቤት በክህሎት በእውቀትና በስነምግባር የታነጸ ትውልድን ለማፍራት አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ገልፀዋል።
በክህሎትና በእውቀት የዳበረ ትውልድ የማፍራት ሀላፊነታችንን ሁላችንም ልንወጣ ይገባልም ብለዋል።

የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ አየለች እሸቴ በበኩላቸው፤ የትምህርት ስብራትን ለመጠገን በርካታ ስራ እየተሰራ መሆኑን ገልጸው፤ በትምህርትና ስልጠና ዜጎችን ወደ ላቀ እውቀት ለማሸጋገር በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አክለዋል።
የኢፌድሪ ቴክኒክና ሙያ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ከድር(ዶ/ር) ዛሬ የተመረቀው ትምህርት ቤት ችግር ፈቺ የሆኑ ዜጎችን ለመፍጠር ያለመ መሆኑን ተናግረዋል።

ትምህርት ቤቱ ታዳጊዎች በክህሎት የዳበረ እውቀት እንዲጨብጡ ለማስቻል ያለመ መሆኑንም ገልጸዋል።
መሰል ሞዴል ትምህርት ቤት መቋቋሙ ለሙያ ትምህርት የሚሰጠውን የተዛባ አስተሳሰብ ለማስተካከል ያለመ መሆኑንም ገልጸዋል።
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025