🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ የካቲት 29/2018 (ኢዜአ)፦ በክህሎት፣ በእውቀትና በስነምግባር የታነፀ ትውልድ ለማፍራት የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የስራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገለፁ።
የኢፌዴሪ ቴክኒክና ሙያ ኢንስቲትዩት በቦሌ አራብሳ አካባቢ ያስገነባውን የቅድመ አንደኛ ትምህርት ቤት ምረቃ እና የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የግንባታ ማስጀመሪያ መርሀግብር አካሂዷል።

የስራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት፣ በክህሎት የዳበሩ ህፃናትና ታዳጊዎችን ለማፍራት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።
ዛሬ የተመረቀው የማህበረሰብ አቀፍ ትምህርት ቤት በክህሎት በእውቀትና በስነምግባር የታነጸ ትውልድን ለማፍራት አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ገልፀዋል።
በክህሎትና በእውቀት የዳበረ ትውልድ የማፍራት ሀላፊነታችንን ሁላችንም ልንወጣ ይገባልም ብለዋል።

የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ አየለች እሸቴ በበኩላቸው፤ የትምህርት ስብራትን ለመጠገን በርካታ ስራ እየተሰራ መሆኑን ገልጸው፤ በትምህርትና ስልጠና ዜጎችን ወደ ላቀ እውቀት ለማሸጋገር በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አክለዋል።
የኢፌድሪ ቴክኒክና ሙያ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ከድር(ዶ/ር) ዛሬ የተመረቀው ትምህርት ቤት ችግር ፈቺ የሆኑ ዜጎችን ለመፍጠር ያለመ መሆኑን ተናግረዋል።

ትምህርት ቤቱ ታዳጊዎች በክህሎት የዳበረ እውቀት እንዲጨብጡ ለማስቻል ያለመ መሆኑንም ገልጸዋል።
መሰል ሞዴል ትምህርት ቤት መቋቋሙ ለሙያ ትምህርት የሚሰጠውን የተዛባ አስተሳሰብ ለማስተካከል ያለመ መሆኑንም ገልጸዋል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026