የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

ዩኒቨርስቲው ለዲጂታል ኢትዮጵያ ስኬት በዘርፉ የተሻለ ክህሎት ያለው የሰው ኃይል ለማፍራት ድርሻውን እየተወጣ ነው

Mar 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሮቤ፤ መጋቢት 12/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ለዲጂታል ኢትዮጵያ ስኬት በዘርፉ የተሻለ ክህሎት ያለው የሰው ኃይል ለማፍራት ድርሻውን እየተወጣ መሆኑን ገለጸ።

ዩኒቨርሲቲው ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በቴክኖሎጂ ፈጠራና ኢንተርፕረነርሺፕ ላይ ያተኮረ ተግባር ተኮር ሥልጠና እየሰጠ ይገኛል።

ይህ ሥልጠና ለዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ግብ ስኬት ጉልህ ድርሻ እንደሚኖረው ተመላክቷል።

የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዚዳንት በዛብህ ወንድሙ (ተባባሪ ፕሮፌሰር) እንደገለጹት፤ ዩኒቨርሲቲው በዲጂታል ቴክኖሎጂ ዘርፍ ብቁ ዜጎችን ለማፍራት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው።


በተለይም በባሌ እና ምስራቅ ባሌ ዞኖችና በምዕራብ አርሲ ዞን በሚገኙ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የቴክኖሎጂ ዝንባሌ ያላቸውን ተማሪዎች በመመልመል የክህሎት ሥልጠና እንዲያገኙ እያደረገ ይገኛል ብለዋል።

ከዚህም ባለፈ በተለያዩ ጊዜያት በሚሰጡ የአቅም ግንባታ ሥልጠናዎች የዜጎችን የሥራ ፈጣሪነት ባህል በሚያሳድግ መልኩ እንዲሰጡ መደረጉንም ገልጸዋል።


በ2017 ዓ.ም በሀገር አቀፍ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ውድድር ዩኒቨርሲቲውን ወክለው የቀረቡ ተማሪዎች አንደኛ ደረጃን በመያዝ ሽልማትና እውቅና ማግኘታቸው የዘርፉ ትኩረት ውጤት መሆኑን ለአብነት አንስተዋል።

በአሁኑ ወቅትም አዲስ የፈጠራ ሀሳብና ግኝት ያላቸው ግለሰቦች በሥራቸው ስኬታማ እንዲሆኑና ሊያጋጥሟቸው የሚችሉ ተግዳሮቶችን እንዲረዱ የአቅም ግንባታ ሥልጠና እየተሰጠ መሆኑን አክለዋል።

ዩኒቨርሲቲው ለዲጂታል ኢትዮጵያ ስኬት በዘርፉ ክህሎት የበለጸገ የሰው ኃይል ለማፍራት ድርሻውን መወጣቱን ይቀጥላል ነው ያሉት።

በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የጀማሪ ሥራ ፈጣሪዎች ኢንተርፕራይዝ ከፍተኛ ባለሙያ ወይዘሮ ራሄል ደበበ በበኩላቸው፤ ዲጂታል ኢትዮጵያ አገልግሎትን ከማዘመን ባለፈ የዜጎችን ተወዳዳሪነት እንደሚያሳድግ ተናግረዋል።

ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ ተግባራትም ተቋማት አገልግሎታቸውን ከቴክኖሎጂ ጋር በማስተሳሰር የዜጎችን ጊዜና ወጪ መቆጠብ መቻሉን አስታውሰዋል።

ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የተሻለ የፈጠራ ሀሳብ ያላቸው ወጣቶች ውጤታማ እንዲሆኑ ከባለድርሻ አካላት ጋር እየሰራ መሆኑንና የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ መድረክም የዚሁ ጥረት አካል መሆኑን ገልጸዋል።


የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሚያዝያ እና ግንቦት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት ከምስል ጋር!

  የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...

Jun 4, 2026

በዲጂታል ክህሎት ራሳችንን እያበቃን ነው - ተማሪዎች

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...

Jun 1, 2026

በኦሮሚያ ክልል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ የአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት ተሰጥቷል

አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...

May 25, 2026

በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው

ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...

May 15, 2026