🔇Unmute
ድሬዳዋ፤ መጋቢት 12/2018 (ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ለአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ በተደረጉ የተቀናጁ ድጋፎች ወደ ማምረት የተመለሱ ኢንዱስትሪዎች ለበርካቶች የሥራ ዕድል መፍጠራቸው ተገለጸ።
የድሬዳዋ አሥተዳደር ምክትል ከንቲባና የንግድ፣ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊ ሀርቢ ቡህ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ባለፉት አራት ዓመታት በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ለአምራች ኢንዱስትሪው በተደረገው ድጋፍና ክትትል በግንባታ ላይ እና ተዘግተው የነበሩ በርካታ ኢንዱስትሪዎች ከ10 ሺህ ለሚልቁ ጎች የሥራ ዕድል ፈጥረዋል።

ኢንዱስትሪዎቹ ተኪ ምርቶችን እና ወደ ውጭ የሚላኩ ምርቶችን በማምረት የውጭ ምንዛሬን የማዳንና የማስገኘት ዐቅማቸው እየጨመረ መምጣቱንም ተናግረዋል።
በሌላ በኩል በያዝነው የበጀት ዓመት ብቻ 11 ኢንዱስትሪዎች ተመርቀው ሥራ መጀመራቸውን ገልጸው፤ ፋብሪካዎቹ ከ1 ሺህ 500 በላይ ለሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠራቸውን አንስተዋል።
ከሁለት ወራት በኋላም ሥድስት ፋብሪካዎችን ወደ ሥራ ለማስገባት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን አስታውቀዋል።

የፌደራልና የአሥተዳደሩ ተቋማት የተካተቱበት ዘርፉን የሚደግፍ አሠራር ተዘርግቶ፤ የኢንዱስትሪዎቹን የዓመታት የፋይናንስ፣ የመሬት፣ የመንገድ፣ የውኃ፣ የኃይልና የአገልግሎት ጥያቄዎችን በፍጥነት የመፍታት ተግባር እየተከናወነ መሆኑም አረጋግጠዋል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026