🔇Unmute
ድሬዳዋ፤ መጋቢት 12/2018 (ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ለአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ በተደረጉ የተቀናጁ ድጋፎች ወደ ማምረት የተመለሱ ኢንዱስትሪዎች ለበርካቶች የሥራ ዕድል መፍጠራቸው ተገለጸ።
የድሬዳዋ አሥተዳደር ምክትል ከንቲባና የንግድ፣ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊ ሀርቢ ቡህ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ባለፉት አራት ዓመታት በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ለአምራች ኢንዱስትሪው በተደረገው ድጋፍና ክትትል በግንባታ ላይ እና ተዘግተው የነበሩ በርካታ ኢንዱስትሪዎች ከ10 ሺህ ለሚልቁ ጎች የሥራ ዕድል ፈጥረዋል።

ኢንዱስትሪዎቹ ተኪ ምርቶችን እና ወደ ውጭ የሚላኩ ምርቶችን በማምረት የውጭ ምንዛሬን የማዳንና የማስገኘት ዐቅማቸው እየጨመረ መምጣቱንም ተናግረዋል።
በሌላ በኩል በያዝነው የበጀት ዓመት ብቻ 11 ኢንዱስትሪዎች ተመርቀው ሥራ መጀመራቸውን ገልጸው፤ ፋብሪካዎቹ ከ1 ሺህ 500 በላይ ለሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠራቸውን አንስተዋል።
ከሁለት ወራት በኋላም ሥድስት ፋብሪካዎችን ወደ ሥራ ለማስገባት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን አስታውቀዋል።

የፌደራልና የአሥተዳደሩ ተቋማት የተካተቱበት ዘርፉን የሚደግፍ አሠራር ተዘርግቶ፤ የኢንዱስትሪዎቹን የዓመታት የፋይናንስ፣ የመሬት፣ የመንገድ፣ የውኃ፣ የኃይልና የአገልግሎት ጥያቄዎችን በፍጥነት የመፍታት ተግባር እየተከናወነ መሆኑም አረጋግጠዋል።
ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...
Aug 28, 2026
መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...
Aug 18, 2026
ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...
Aug 10, 2026
አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...
Jul 20, 2026