🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 12/2018 (ኢዜአ)፡- የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር የኢትዮጵያን የደን ሽፋን በማሳደግ ዘርፈ-ብዙ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎችን እያበረከተ መሆኑን የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ አስገነዘቡ።
የፌዴራልና የክልል የግብርና ዘርፍ የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ''የመደመር መንግሥት የተፈጥሮ ሃብት ዕይታ'' በሚል መሪ ሐሳብ የዓለም የደን ቀንን አስመልክቶ የምክክር መድረክ እየተካሄደ ነው።

ሚኒስትር አዲሱ አረጋ በዚሁ ወቅት፤ የመደመር መንግሥት ለአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር የሰጠው ትኩረት የተፈጥሮ ሃብቶችን በማስጠበቅ ዘርፈ-ብዙ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ማበርከት ያስቻሉ ውጤቶች ማስገኘቱን አስገንዝበዋል።
በዚህም ባለፉት የለውጥ ዓመታት ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞችን በመትከል የኢትዮጵያን የደን ሽፋን ከነበረበት የ17 ነጥብ 3 በመቶ ወደ 23 ነጥብ 6 በመቶ ማሳደግ እንደተቻለ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያን የተራቆተ የመሬት ገፅታ በደን በመሸፈን የአፈር መሸርሸርና የሥነ-ምኅዳር ደኅንነትን መጠበቅ ያስቻለ ውጤት እየተገኘ መሆኑንም አንስተዋል።

ቡናን ጨምሮ በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር የሚተከሉ ችግኞች የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ ዘርፈ-ብዙ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ እያበረከቱ እንደሚገኙም አረጋግጠዋል።
በቀጣይም የማኅበረሰቡን የደን ጥበቃ ግንዛቤ በማሳደግና የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር በማስቀጠል በትኩረት እንደሚሠራ አመላክተዋል።
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025
ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...
Feb 8, 2025