የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር በርካታ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎችን እያበረከተ ነው

Mar 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 12/2018 (ኢዜአ)፡- የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር የኢትዮጵያን የደን ሽፋን በማሳደግ ዘርፈ-ብዙ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎችን እያበረከተ መሆኑን የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ አስገነዘቡ።

የፌዴራልና የክልል የግብርና ዘርፍ የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ''የመደመር መንግሥት የተፈጥሮ ሃብት ዕይታ'' በሚል መሪ ሐሳብ የዓለም የደን ቀንን አስመልክቶ የምክክር መድረክ እየተካሄደ ነው።


ሚኒስትር አዲሱ አረጋ በዚሁ ወቅት፤ የመደመር መንግሥት ለአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር የሰጠው ትኩረት የተፈጥሮ ሃብቶችን በማስጠበቅ ዘርፈ-ብዙ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ማበርከት ያስቻሉ ውጤቶች ማስገኘቱን አስገንዝበዋል።

በዚህም ባለፉት የለውጥ ዓመታት ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞችን በመትከል የኢትዮጵያን የደን ሽፋን ከነበረበት የ17 ነጥብ 3 በመቶ ወደ 23 ነጥብ 6 በመቶ ማሳደግ እንደተቻለ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያን የተራቆተ የመሬት ገፅታ በደን በመሸፈን የአፈር መሸርሸርና የሥነ-ምኅዳር ደኅንነትን መጠበቅ ያስቻለ ውጤት እየተገኘ መሆኑንም አንስተዋል።


ቡናን ጨምሮ በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር የሚተከሉ ችግኞች የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ ዘርፈ-ብዙ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ እያበረከቱ እንደሚገኙም አረጋግጠዋል።

በቀጣይም የማኅበረሰቡን የደን ጥበቃ ግንዛቤ በማሳደግና የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር በማስቀጠል በትኩረት እንደሚሠራ አመላክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.