🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 12/2018 (ኢዜአ)፡- የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር የኢትዮጵያን የደን ሽፋን በማሳደግ ዘርፈ-ብዙ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎችን እያበረከተ መሆኑን የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ አስገነዘቡ።
የፌዴራልና የክልል የግብርና ዘርፍ የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ''የመደመር መንግሥት የተፈጥሮ ሃብት ዕይታ'' በሚል መሪ ሐሳብ የዓለም የደን ቀንን አስመልክቶ የምክክር መድረክ እየተካሄደ ነው።

ሚኒስትር አዲሱ አረጋ በዚሁ ወቅት፤ የመደመር መንግሥት ለአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር የሰጠው ትኩረት የተፈጥሮ ሃብቶችን በማስጠበቅ ዘርፈ-ብዙ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ማበርከት ያስቻሉ ውጤቶች ማስገኘቱን አስገንዝበዋል።
በዚህም ባለፉት የለውጥ ዓመታት ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞችን በመትከል የኢትዮጵያን የደን ሽፋን ከነበረበት የ17 ነጥብ 3 በመቶ ወደ 23 ነጥብ 6 በመቶ ማሳደግ እንደተቻለ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያን የተራቆተ የመሬት ገፅታ በደን በመሸፈን የአፈር መሸርሸርና የሥነ-ምኅዳር ደኅንነትን መጠበቅ ያስቻለ ውጤት እየተገኘ መሆኑንም አንስተዋል።

ቡናን ጨምሮ በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር የሚተከሉ ችግኞች የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ ዘርፈ-ብዙ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ እያበረከቱ እንደሚገኙም አረጋግጠዋል።
በቀጣይም የማኅበረሰቡን የደን ጥበቃ ግንዛቤ በማሳደግና የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር በማስቀጠል በትኩረት እንደሚሠራ አመላክተዋል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026