🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ሳዑዲ አረቢያ በንግድና ገበያ ዕድል ድርድር ዙሪያ ምክክር አድርገዋል።
14ኛው የዓለም ንግድ ድርጅት(WTO) የሚኒስትሮች ጉባኤ (MC14) በካሜሮን ያውንዴ እየተካሄደ ይገኛል።
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) ከጉባኤው ጎን ለጎን ከሳዑዲ አረቢያ የዓለም አቀፍ ስምምነቶችና ድርጅቶች ምክትል ገዥ እና የድርድር ቡድን መሪ ፋሪድ አል-አሳሊ ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል።

ውይይቱ በዋናነት ያተኮረው በሁለቱ ሀገራት መካከል ባለው የገበያ ዕድል ድርድርና የንግድ ልውውጥን ይበልጥ ማሳደግ በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ ነው።
ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ ወደ ዓለም ንግድ ድርጅት ለመቀላቀል የምታደርገውን ድርድር በፈረንጆቹ 2026 ለማጠናቀቅ ያላትን ጽኑ አቋምና ዝግጁነት አብራርተዋል።
ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባል ለመሆን የምታደርገው ጥረት ማጠናቀቂያው ላይ በደረሰበት በዚህ ወቅት፣ እንደ ሳዑዲ አረቢያ ካሉ ጠንካራ የንግድ አጋሮች ጋር የሚደረጉ የሁለትዮሽ ድርድሮች ለሀገሪቱ የኢኮኖሚ እድገትና ለንግድ ስርዓቱ መዘመን ትልቅ ፋይዳ እንዳላቸው ተገልጿል።

በመጪው ሚያዚያ ወር በጄኔቫ ከሚካሄደው የሥራ ቡድን ስብሰባ በፊት የሁለትዮሽ የገበያ ዕድል ስምምነቱን ለማጠናቀቅ ቀጣይ የቴክኒክ ድርድሮች በፍጥነት እንዲከወኑ በሁለቱ ወገኖች መካከል መግባባት ላይ ተደርሷል።
ዲፕሎማሲያዊ ጥረቱ ኢትዮጵያ ወደ ዓለም አቀፍ የንግድ ሥርዓት ለመቀላቀል የምታደርገውን ጉዞ የሚያፋጥንና የሀገሪቱን የንግድ ጥቅሞች ይበልጥ የሚያረጋግጥ መሆኑን ኢዜአ ከንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...
Aug 28, 2026
መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...
Aug 18, 2026
ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...
Aug 10, 2026
አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...
Jul 20, 2026