የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የተሰማራንበት የፍራፍሬና አትክልት ልማት ተጠቃሚ አድርጎናል-አርሶ አደሮች

Mar 31, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሀላባ ቁሊቶ፤መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦በፍራፍሬና አትክልት ልማት በመሰማራታቸው ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸው ማደጉን በሀላባ ዞን የዌራ ዲጆ ወረዳ አርሶ አደሮች ገለጹ።


የዌራ ዲጆ ወረዳ ከዚህ ቀደም በጎርፍ አደጋና በመሬት ተዳፋትነት ምክንያት ለልማት አስቸጋሪ የነበረ ቢሆንም፣በአሁኑ ወቅት ግን በተከታታይ የአካባቢ ጥበቃ ስራ በመሰራቱ መሬቱ የተሻለ ምርት እየሰጠ መሆኑም ተገልጿል።


ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡ የወረዳው አርሶ አደሮች እንደገለፁት፥ ቀደም ሲል አካባቢው ዝናብ በዘነበ ቁጥር ለጎርፍ ተጋላጭ በመሆኑ አርሶ አደሩ እርዳታ ጠባቂ ሆኖ ቆይቷል።


በአካባቢው የጎርፍ መቀልበሻ ግንባታ በመከናወኑ እና በሶላር ሃይል የሚሰራ የከርሰ ምድር ውሃ ጥቅም ላይ እንዲውል በመደረጉ፣ አካባቢው ዛሬ ላይ የሌሎች ተሞክሮ መቅሰሚያ ማዕከል ለመሆን በቅቷል ብለዋል።


በኩታ ገጠም በመደራጀት አትክልትና ፍራፍሬ በማልማት ላይ የሚገኙ አርሶ አደሮች "ቀደም ሲል በሴፍቲኔት እርዳታ እንኖር ነበር፤ አሁን ግን በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ ምርታችንን ለገበያ በማቅረብ ህይወታችንን እየለወጥን ነው" ብለዋል።


ሌላው የመንገሳ ኢንተርፕራይዝ አባል ዱባለ ሁሴን፤ አምስት ሆነው በተደራጁ በስድስት ወራት ውስጥ በ4 ነጥብ 5 ሄክታር መሬት ላይ የተለያዩ የጓሮ አትክልቶችን በማልማት ተጠቃሚ መሆን መጀመራቸውን ገልጿል።


በአካባቢው በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት የተሰማራ የእርሻ ድርጅት ስራ አስኪያጅ አደም ኑርአብደላ፤ በ30 ሄክታር መሬት ላይ በመስኖ ልማት እየሰሩ መሆኑን ገልጸው፣ ከዚህ ውስጥ በ4 ሄክታር ላይ አቮካዶና ሙዝ በማልማት ውጤት ማግኘት መጀመራቸውን ተናግረዋል።


ልማቱ ለአካባቢው ነዋሪዎች የሥራ ዕድል ከመፍጠሩም በላይ ምርትን በተመጣጣኝ ዋጋ ለህብረተሰቡ እያቀረበ ይገኛል።


የሀላባ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና መምሪያ ሃላፊ አቶ ሀጂ ኑሪዬ እንደገለጹት፥ ወረዳውን ከእርዳታ ጠባቂነት ለማውጣት ሰፊ ስራ ተሰርቷል።


"በ13 ቀበሌዎች ይከሰት የነበረውን ጎርፍ ለመከላከል ከ6 ኪሎ ሜትር በላይ የጎርፍ መቀልበሻ ተገንብቷል ብለዋል።


በተጨማሪም ከ86 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ የከርሰ ምድር ውሃን በሶላር ሃይል ለመስኖ እንዲውል ተደርጓል" ነው ያሉት።


ይህም አርሶ አደሩ ከችግር ወጥቶ የምግብ ዋስትናውን እንዲያረጋግጥ ትልቅ አስተዋጽኦ ማድረጉን አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሚያዝያ እና ግንቦት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት ከምስል ጋር!

  የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...

Jun 4, 2026

በዲጂታል ክህሎት ራሳችንን እያበቃን ነው - ተማሪዎች

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...

Jun 1, 2026

በኦሮሚያ ክልል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ የአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት ተሰጥቷል

አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...

May 25, 2026

በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው

ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...

May 15, 2026