የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የተሰማራንበት የፍራፍሬና አትክልት ልማት ተጠቃሚ አድርጎናል-አርሶ አደሮች

Mar 31, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሀላባ ቁሊቶ፤መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦በፍራፍሬና አትክልት ልማት በመሰማራታቸው ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸው ማደጉን በሀላባ ዞን የዌራ ዲጆ ወረዳ አርሶ አደሮች ገለጹ።


የዌራ ዲጆ ወረዳ ከዚህ ቀደም በጎርፍ አደጋና በመሬት ተዳፋትነት ምክንያት ለልማት አስቸጋሪ የነበረ ቢሆንም፣በአሁኑ ወቅት ግን በተከታታይ የአካባቢ ጥበቃ ስራ በመሰራቱ መሬቱ የተሻለ ምርት እየሰጠ መሆኑም ተገልጿል።


ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡ የወረዳው አርሶ አደሮች እንደገለፁት፥ ቀደም ሲል አካባቢው ዝናብ በዘነበ ቁጥር ለጎርፍ ተጋላጭ በመሆኑ አርሶ አደሩ እርዳታ ጠባቂ ሆኖ ቆይቷል።


በአካባቢው የጎርፍ መቀልበሻ ግንባታ በመከናወኑ እና በሶላር ሃይል የሚሰራ የከርሰ ምድር ውሃ ጥቅም ላይ እንዲውል በመደረጉ፣ አካባቢው ዛሬ ላይ የሌሎች ተሞክሮ መቅሰሚያ ማዕከል ለመሆን በቅቷል ብለዋል።


በኩታ ገጠም በመደራጀት አትክልትና ፍራፍሬ በማልማት ላይ የሚገኙ አርሶ አደሮች "ቀደም ሲል በሴፍቲኔት እርዳታ እንኖር ነበር፤ አሁን ግን በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ ምርታችንን ለገበያ በማቅረብ ህይወታችንን እየለወጥን ነው" ብለዋል።


ሌላው የመንገሳ ኢንተርፕራይዝ አባል ዱባለ ሁሴን፤ አምስት ሆነው በተደራጁ በስድስት ወራት ውስጥ በ4 ነጥብ 5 ሄክታር መሬት ላይ የተለያዩ የጓሮ አትክልቶችን በማልማት ተጠቃሚ መሆን መጀመራቸውን ገልጿል።


በአካባቢው በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት የተሰማራ የእርሻ ድርጅት ስራ አስኪያጅ አደም ኑርአብደላ፤ በ30 ሄክታር መሬት ላይ በመስኖ ልማት እየሰሩ መሆኑን ገልጸው፣ ከዚህ ውስጥ በ4 ሄክታር ላይ አቮካዶና ሙዝ በማልማት ውጤት ማግኘት መጀመራቸውን ተናግረዋል።


ልማቱ ለአካባቢው ነዋሪዎች የሥራ ዕድል ከመፍጠሩም በላይ ምርትን በተመጣጣኝ ዋጋ ለህብረተሰቡ እያቀረበ ይገኛል።


የሀላባ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና መምሪያ ሃላፊ አቶ ሀጂ ኑሪዬ እንደገለጹት፥ ወረዳውን ከእርዳታ ጠባቂነት ለማውጣት ሰፊ ስራ ተሰርቷል።


"በ13 ቀበሌዎች ይከሰት የነበረውን ጎርፍ ለመከላከል ከ6 ኪሎ ሜትር በላይ የጎርፍ መቀልበሻ ተገንብቷል ብለዋል።


በተጨማሪም ከ86 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ የከርሰ ምድር ውሃን በሶላር ሃይል ለመስኖ እንዲውል ተደርጓል" ነው ያሉት።


ይህም አርሶ አደሩ ከችግር ወጥቶ የምግብ ዋስትናውን እንዲያረጋግጥ ትልቅ አስተዋጽኦ ማድረጉን አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026