የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በክልሉ ባለፉት የለውጥ ዓመታት የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ የልማት ስራዎች ተከናውነዋል

Apr 3, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አምቦ፤ መጋቢት 24/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ባለፉት የለውጥ ዓመታት የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ የልማት ስራዎች ተከናውነዋል ሲሉ የክልሉ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አወሉ አብዲ ተናገሩ።

ለውጡን ምክንያት በማድረግ በምዕራብ ሸዋ ዞንና በአምቦ ከተማ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የተሳተፉበት የድጋፍ ሰልፍ ተካሂዷል።


በህዝባዊ ሰልፉ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት አቶ አወሉ አብዲ፤ በክልሉ ባለፉት የለውጥ ዓመታት የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ የልማት ስራዎች ተከናውነዋል ብለዋል።

በእነዚህ ዓመታት በየአካባቢው ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች መከናወናቸውን ጠቅሰው፣ በተለይም በኢኮኖሚው ዘርፍ ውጤታማ ስራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል።

በግብርናው ዘርፍ ከባህላዊ የአስተራረስ ዘዴ በመውጣትና በሜካናይዜሽን በመታገዝ ራስን በምግብ ከመቻል ባለፈ ምርትን ለውጭ ገበያ ማቅረብ ተችሏል ነው ያሉት።

በከተማ ልማትም ከተማዎችን በቴክኖሎጂ ከማዘመን ባለፈ የ"አንድ ማዕከል" አገልግሎት በማስጀመር ህዝቡ ቀልጣፋና ጥራት ያለው አገልግሎት እንዲያገኝ ተደርጓል ብለዋል።

በለውጡ ዓመታት የተመዘገቡ የልማት ስኬቶችን ለማስቀጠል ዘላቂ ሰላምን በማረጋገጥ ህዝቡ በአንድነት ሊቆም እንደሚገባ አሳስበዋል።


የምዕራብ ሸዋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዲዳ ጉደታ በበኩላቸው፤ የለውጡ መንግስት ቀደም ሲል የነበሩ ውስብስብ የኢኮኖሚና ማህበራዊ ችግሮችን በመፍታት ትላልቅ ፕሮጀክቶችን ማከናወኑን ገልጸዋል።

ዘንድሮም በ6ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለህዝብ የገባነውን ቃል አክብረን፣ ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ አዲስ ቃልኪዳን የምንገባበትና የተጀመሩ ልማቶችን የምናስቀጥልበት ነው ብለዋል።


የአምቦ ከተማ ከንቲባ አቶ ሃጫሉ ገመቹ፤ በከተማው ከመጋቢት 24 ቀን 2010 ዓ.ም በኋላ በሁሉም የልማት ዘርፎች የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆናቸውን ተናግረዋል።

በድጋፍ ሰልፉ ላይ የተሳተፉ ነዋሪዎችም በለውጡ ዓመታት በተመዘገቡ የልማት ስራዎች ተሳታፊ እና ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ወጣት ዳግማዊት ቁምላቸው፤ የተገኙ ስኬቶችን በመጠበቅና የአካባቢውን ሰላም በማስጠበቅ የሀገሪቱን እድገት ለማፋጠን ዝግጁ መሆኗን ገልጻለች።


ሌሎች ወጣቶችም ለሀገራቸው እድገት በጋራ እንዲሰሩ ጥሪ አቅርባለች።


አቶ ንጉሴ ጆሮ በበኩላቸው፤ ህብረተሰቡ በአንድነት በመቆም ለሰላምና ለልማት አስተዋጽኦውን ማስቀጠል ይጠበቅበታል ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሚያዝያ እና ግንቦት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት ከምስል ጋር!

  የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...

Jun 4, 2026

በዲጂታል ክህሎት ራሳችንን እያበቃን ነው - ተማሪዎች

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...

Jun 1, 2026

በኦሮሚያ ክልል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ የአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት ተሰጥቷል

አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...

May 25, 2026

በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው

ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...

May 15, 2026