የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የሀገራዊ ለውጡ አዲስ ምዕራፍ - የመንገድ መሰረተ ልማት

Apr 8, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

መጋቢት 24 በኢትዮጵያ የፖለቲካ ውስጥ አዲስ ምዕራፍን የከፈተ የለውጥ ምዕራፍ ጅማሮ ማብሰሪያ ነው።

ለውጡም በፈተናዎች ውስጥ ኢትዮጵያን ወደ ከፍታ የሚያሻግሩ በርካታ ስኬቶችን በማስመዝገብ ዘልቋል፡፡

ላለፉት 8 የለውጥ አመታት ትኩረት ከተሰጣቸው ዘርፎች መካከል አንዱ የመንገድ መሰረተ ልማት ነው።

በሀረሪ ክልልም ለመንገድ መሰረተ ልማት በተሰጠው ትኩረትና በተከናወኑ ተግባራት የህዝቡን የመንገድ መሰረተ ልማት ችግር የቀረፉ በርካታ ስኬቶች መመዝገባቸውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ አስታውቋል።


በተለይም ገጠሩን ከከተማው ጋር በማስተሳሰር በከተማ እና ገጠር ፍትሀዊ የሆነ የመሰረተ ልማት ተደራሽነት እንዲኖር ለማስቻል ዘርፈ ብዙ ስራዎች መከናወናቸውን ገልጿል።

በዚህም ወረዳን ከወረዳ ብሎም ገጠሩን ከከተማ ጋር የሚያገናኙ የአስፓልት እና የጠጠር መንገዶች ተገንብተው ለአገልግሎት ክፍት ተደርገዋል።

ይህም አርሶ አደሩ ምርቱን በቀላሉ ለገበያ ማቅረብ እንዲችል፤ እንግልትና የምርት ብክነት መቀነሱ ተመላክቷል።

በከተማም የተገነቡ የመንገድ መሰረተ ልማቶች የትራንስፖርት እንቅስቃሴው የተሳለጠ እንዲሆን ከማስቻል በተጨማሪ የተገነቡ ምቹ የእግረኛ መንገዶች የዜጎችን ደህንነት ከማረጋገጥ ባሻገር ከተማዋን የተሻለ ገፅታ አላብሰዋል።


የመንገድ ፕሮጀክቶቹ ገፅታ ከመቀየር ባሻገር የየአካባቢው ኢኮኖሚ እንዲነቃቃ ማድረጉ ተገልጿል።

የለውጡ መንግሥት ለህዝቡ ቃል በገባው መሰረት ፕሮጀክቶችን በአጭር ግዜ ጀምሮ በጥራት እና ፍጥነት ማጠናቀቅ መገለጫው ሆኗል።

እውን የሆኑ ፕሮጀክቶች ጊዜን ብቻ ማእከል ያደረጉ ሳይሆኑ ጥራትን ጨምረው ዘመን ተሻጋሪነትን ማዕከል ተደረገው የተገነቡ ናቸው።


በለውጡ አመታት በመንገድ መሰረተ ልማት የተሰሩ ስራዎችም ህዝቡ ለዘመናት ሲያነሳቸው የቆዩ ጥያቄዎች ምላሽ እንዲያገኝ ያስቻሉ መሆናቸውን ነው ቢሮው ያስታወቀው።

የክልሉ መንግስት ለመንገድ መሰረተ ልማት ልዩ ትኩረት በመስጠት እያከናወናቸው የሚገኙ ስራዎችን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጿል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026

<p>ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በቦንጋ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው</p>

ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...

Feb 24, 2025

<p>በክልሉ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ እየተካሄደ ነው</p>

ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...

Feb 24, 2025

<p>በሚቀጥሉት አምስት አመታት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይት በተሻለ መልኩ ስራ ላይ ይውላል - የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...

Feb 8, 2025