🔇Unmute
መጋቢት 24 በኢትዮጵያ የፖለቲካ ውስጥ አዲስ ምዕራፍን የከፈተ የለውጥ ምዕራፍ ጅማሮ ማብሰሪያ ነው።
ለውጡም በፈተናዎች ውስጥ ኢትዮጵያን ወደ ከፍታ የሚያሻግሩ በርካታ ስኬቶችን በማስመዝገብ ዘልቋል፡፡
ላለፉት 8 የለውጥ አመታት ትኩረት ከተሰጣቸው ዘርፎች መካከል አንዱ የመንገድ መሰረተ ልማት ነው።
በሀረሪ ክልልም ለመንገድ መሰረተ ልማት በተሰጠው ትኩረትና በተከናወኑ ተግባራት የህዝቡን የመንገድ መሰረተ ልማት ችግር የቀረፉ በርካታ ስኬቶች መመዝገባቸውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ አስታውቋል።

በተለይም ገጠሩን ከከተማው ጋር በማስተሳሰር በከተማ እና ገጠር ፍትሀዊ የሆነ የመሰረተ ልማት ተደራሽነት እንዲኖር ለማስቻል ዘርፈ ብዙ ስራዎች መከናወናቸውን ገልጿል።
በዚህም ወረዳን ከወረዳ ብሎም ገጠሩን ከከተማ ጋር የሚያገናኙ የአስፓልት እና የጠጠር መንገዶች ተገንብተው ለአገልግሎት ክፍት ተደርገዋል።
ይህም አርሶ አደሩ ምርቱን በቀላሉ ለገበያ ማቅረብ እንዲችል፤ እንግልትና የምርት ብክነት መቀነሱ ተመላክቷል።
በከተማም የተገነቡ የመንገድ መሰረተ ልማቶች የትራንስፖርት እንቅስቃሴው የተሳለጠ እንዲሆን ከማስቻል በተጨማሪ የተገነቡ ምቹ የእግረኛ መንገዶች የዜጎችን ደህንነት ከማረጋገጥ ባሻገር ከተማዋን የተሻለ ገፅታ አላብሰዋል።

የመንገድ ፕሮጀክቶቹ ገፅታ ከመቀየር ባሻገር የየአካባቢው ኢኮኖሚ እንዲነቃቃ ማድረጉ ተገልጿል።
የለውጡ መንግሥት ለህዝቡ ቃል በገባው መሰረት ፕሮጀክቶችን በአጭር ግዜ ጀምሮ በጥራት እና ፍጥነት ማጠናቀቅ መገለጫው ሆኗል።
እውን የሆኑ ፕሮጀክቶች ጊዜን ብቻ ማእከል ያደረጉ ሳይሆኑ ጥራትን ጨምረው ዘመን ተሻጋሪነትን ማዕከል ተደረገው የተገነቡ ናቸው።

በለውጡ አመታት በመንገድ መሰረተ ልማት የተሰሩ ስራዎችም ህዝቡ ለዘመናት ሲያነሳቸው የቆዩ ጥያቄዎች ምላሽ እንዲያገኝ ያስቻሉ መሆናቸውን ነው ቢሮው ያስታወቀው።
የክልሉ መንግስት ለመንገድ መሰረተ ልማት ልዩ ትኩረት በመስጠት እያከናወናቸው የሚገኙ ስራዎችን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጿል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026