🔇Unmute
መጋቢት 24 በኢትዮጵያ የፖለቲካ ውስጥ አዲስ ምዕራፍን የከፈተ የለውጥ ምዕራፍ ጅማሮ ማብሰሪያ ነው።
ለውጡም በፈተናዎች ውስጥ ኢትዮጵያን ወደ ከፍታ የሚያሻግሩ በርካታ ስኬቶችን በማስመዝገብ ዘልቋል፡፡
ላለፉት 8 የለውጥ አመታት ትኩረት ከተሰጣቸው ዘርፎች መካከል አንዱ የመንገድ መሰረተ ልማት ነው።
በሀረሪ ክልልም ለመንገድ መሰረተ ልማት በተሰጠው ትኩረትና በተከናወኑ ተግባራት የህዝቡን የመንገድ መሰረተ ልማት ችግር የቀረፉ በርካታ ስኬቶች መመዝገባቸውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ አስታውቋል።

በተለይም ገጠሩን ከከተማው ጋር በማስተሳሰር በከተማ እና ገጠር ፍትሀዊ የሆነ የመሰረተ ልማት ተደራሽነት እንዲኖር ለማስቻል ዘርፈ ብዙ ስራዎች መከናወናቸውን ገልጿል።
በዚህም ወረዳን ከወረዳ ብሎም ገጠሩን ከከተማ ጋር የሚያገናኙ የአስፓልት እና የጠጠር መንገዶች ተገንብተው ለአገልግሎት ክፍት ተደርገዋል።
ይህም አርሶ አደሩ ምርቱን በቀላሉ ለገበያ ማቅረብ እንዲችል፤ እንግልትና የምርት ብክነት መቀነሱ ተመላክቷል።
በከተማም የተገነቡ የመንገድ መሰረተ ልማቶች የትራንስፖርት እንቅስቃሴው የተሳለጠ እንዲሆን ከማስቻል በተጨማሪ የተገነቡ ምቹ የእግረኛ መንገዶች የዜጎችን ደህንነት ከማረጋገጥ ባሻገር ከተማዋን የተሻለ ገፅታ አላብሰዋል።

የመንገድ ፕሮጀክቶቹ ገፅታ ከመቀየር ባሻገር የየአካባቢው ኢኮኖሚ እንዲነቃቃ ማድረጉ ተገልጿል።
የለውጡ መንግሥት ለህዝቡ ቃል በገባው መሰረት ፕሮጀክቶችን በአጭር ግዜ ጀምሮ በጥራት እና ፍጥነት ማጠናቀቅ መገለጫው ሆኗል።
እውን የሆኑ ፕሮጀክቶች ጊዜን ብቻ ማእከል ያደረጉ ሳይሆኑ ጥራትን ጨምረው ዘመን ተሻጋሪነትን ማዕከል ተደረገው የተገነቡ ናቸው።

በለውጡ አመታት በመንገድ መሰረተ ልማት የተሰሩ ስራዎችም ህዝቡ ለዘመናት ሲያነሳቸው የቆዩ ጥያቄዎች ምላሽ እንዲያገኝ ያስቻሉ መሆናቸውን ነው ቢሮው ያስታወቀው።
የክልሉ መንግስት ለመንገድ መሰረተ ልማት ልዩ ትኩረት በመስጠት እያከናወናቸው የሚገኙ ስራዎችን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጿል።
ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...
Aug 28, 2026
መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...
Aug 18, 2026
ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...
Aug 10, 2026
አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...
Jul 20, 2026