የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ላለፉት 80 ዓመታት የዕድገትና የሀገር ኩራት ምሳሌ ሆኖ ቀጥሏል

Apr 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ አየር መንገድ ላለፉት 80 ዓመታት የዕድገት፣ የትርፋማነት እና የሀገር ኩራት ምሳሌ ሆኖ መዝለቁን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ መስፍን ጣሰው ገለፁ።

አየር መንገዱ ፈተናዎች በጽናት በማለፍ አፍሪካን ከዓለም ጋር የሚያገናኝ ቀዳሚ የአቪዬሽን ተቋም መሆኑን በተግባር ማረጋገጡንም ጠቅሰዋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ 80ኛ ዓመት የምስረታ በዓልን አስመልክቶ የአየር መንገዱ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል።

ዋና ስራ አስፈፃሚው፤ ተቋሙ ባለፋት ስምንት አስርት ዓመታት የኢትዮጵያ የዕድገት፣ የትርፋማነት እና የሀገር ኩራት ምሳሌ ሆኖ መዝለቁን ገልጸዋል።

አየር መንገዱ የመጀመሪያ በረራውን መጋቢት 30 ቀን 1938 ዓ.ም ማድረጉን ያስታወሱት ዋና ሥራ አስፈፃሚው፤ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ በነበሩት ዓመታት ባስመዘገበው ተከታታይ ዕድገት በአሁኑ ወቅት በዓለም አቀፍ ደረጃ 145 መዳረሻዎች ያሉት ግዙፍ አየር መንገድ ለመሆን መብቃቱን ተናግረዋል።

አየር መንገዱ ዘመኑ ያፈራቸውን እጅግ ዘመናዊ አውሮፕላኖች በመጠቀም ለደንበኞቹ የላቀ አገልግሎት እያቀረበ እንደሚገኝ ጠቅሰው፥ በተለይም በተቋም ግንባታ ረገድ አበረታች ውጤቶች መመዝገባቸውን አስረድተዋል።

በአሁኑ ወቅት የራሱን አውሮፕላኖች ጥገና ማከናወን የሚያስችል ሙሉ አቅም የፈጠረ ሲሆን ይህም ለኩባንያው ዘላቂ ዕድገት ትልቅ መሠረት መጣሉን አመላክተዋል።

የአቪዬሽን ባለሙያዎችን ለማፍራት የራሱ አቪዬሽን አካዳሚ ያለው አየር መንገዱ፥ የአፍሪካ ትልቁን የአቪዬሽን ዩኒቨርሲቲ በመገንባት በታሪኩ ጉልህ ስፍራ የሚሰጠው ስኬት ማስመዝገቡን ገልጸዋል።

አየር መንገዱ ራዕዩን መሸከም የሚችል ብቁ የሰው ኃይል ማፍራት እና የሥራ ሥነ-ምግባር ያለው ታታሪ ሠራተኛ በመፍጠር ረገድ ውጤታማ መሆኑን ተናግረዋል።

የካርጎ የጭነት አገልግሎት አቅሙን ከማሳደጉም በላይ በርካታ ደጋፊ መሠረተ ልማቶችን ገንብቷል ብለዋል።

እነዚህ የተቀናጁ የመሠረተ ልማት ግንባታዎችና የደንበኞችን እርካታ ታሳቢ ያደረጉ አሰራሮች አየር መንገዱ በዓለም አቀፍ የገበያ ውድድር ውስጥ ተወዳዳሪ ሆኖ እንዲቀጥልና አስተማማኝ ዕድገት እንዲያስመዘግብ አስችለውታል ነው ያሉት።

አየር መንገዱ 150 አውሮፕላኖች ያሉት ሲሆን የበረራ ተደራሽነቱንና ጥራቱን ይበልጥ ለማሳደግ 117 አዳዲስ አውሮፕላኖችን ለመግዛት በሂደት ላይ መሆኑን ጠቁመዋል።

ያለፉት ሰማንያ ዓመታት ለአየር መንገዱ የታታሪነት፣ የጠንክሮ መስራት እና የስኬት ዘመናት መሆናቸውን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የገጠሙትን ፈተናዎች በጽናት በማለፍ አፍሪካን ከዓለም ጋር የሚያገናኝ ቀዳሚ የአቪዬሽን ተቋም መሆኑን በተግባር ማረጋገጡን ጠቅሰዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ ነው -ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚው ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለአፍሪካ አገራት ትልቅ አርአያ ናቸው - የላይቤሪያ ልዑካን ቡድን

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...

Apr 16, 2026

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026

<p>ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በቦንጋ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው</p>

ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...

Feb 24, 2025