የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ላለፉት 80 ዓመታት የዕድገትና የሀገር ኩራት ምሳሌ ሆኖ ቀጥሏል

Apr 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ አየር መንገድ ላለፉት 80 ዓመታት የዕድገት፣ የትርፋማነት እና የሀገር ኩራት ምሳሌ ሆኖ መዝለቁን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ መስፍን ጣሰው ገለፁ።

አየር መንገዱ ፈተናዎች በጽናት በማለፍ አፍሪካን ከዓለም ጋር የሚያገናኝ ቀዳሚ የአቪዬሽን ተቋም መሆኑን በተግባር ማረጋገጡንም ጠቅሰዋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ 80ኛ ዓመት የምስረታ በዓልን አስመልክቶ የአየር መንገዱ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል።

ዋና ስራ አስፈፃሚው፤ ተቋሙ ባለፋት ስምንት አስርት ዓመታት የኢትዮጵያ የዕድገት፣ የትርፋማነት እና የሀገር ኩራት ምሳሌ ሆኖ መዝለቁን ገልጸዋል።

አየር መንገዱ የመጀመሪያ በረራውን መጋቢት 30 ቀን 1938 ዓ.ም ማድረጉን ያስታወሱት ዋና ሥራ አስፈፃሚው፤ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ በነበሩት ዓመታት ባስመዘገበው ተከታታይ ዕድገት በአሁኑ ወቅት በዓለም አቀፍ ደረጃ 145 መዳረሻዎች ያሉት ግዙፍ አየር መንገድ ለመሆን መብቃቱን ተናግረዋል።

አየር መንገዱ ዘመኑ ያፈራቸውን እጅግ ዘመናዊ አውሮፕላኖች በመጠቀም ለደንበኞቹ የላቀ አገልግሎት እያቀረበ እንደሚገኝ ጠቅሰው፥ በተለይም በተቋም ግንባታ ረገድ አበረታች ውጤቶች መመዝገባቸውን አስረድተዋል።

በአሁኑ ወቅት የራሱን አውሮፕላኖች ጥገና ማከናወን የሚያስችል ሙሉ አቅም የፈጠረ ሲሆን ይህም ለኩባንያው ዘላቂ ዕድገት ትልቅ መሠረት መጣሉን አመላክተዋል።

የአቪዬሽን ባለሙያዎችን ለማፍራት የራሱ አቪዬሽን አካዳሚ ያለው አየር መንገዱ፥ የአፍሪካ ትልቁን የአቪዬሽን ዩኒቨርሲቲ በመገንባት በታሪኩ ጉልህ ስፍራ የሚሰጠው ስኬት ማስመዝገቡን ገልጸዋል።

አየር መንገዱ ራዕዩን መሸከም የሚችል ብቁ የሰው ኃይል ማፍራት እና የሥራ ሥነ-ምግባር ያለው ታታሪ ሠራተኛ በመፍጠር ረገድ ውጤታማ መሆኑን ተናግረዋል።

የካርጎ የጭነት አገልግሎት አቅሙን ከማሳደጉም በላይ በርካታ ደጋፊ መሠረተ ልማቶችን ገንብቷል ብለዋል።

እነዚህ የተቀናጁ የመሠረተ ልማት ግንባታዎችና የደንበኞችን እርካታ ታሳቢ ያደረጉ አሰራሮች አየር መንገዱ በዓለም አቀፍ የገበያ ውድድር ውስጥ ተወዳዳሪ ሆኖ እንዲቀጥልና አስተማማኝ ዕድገት እንዲያስመዘግብ አስችለውታል ነው ያሉት።

አየር መንገዱ 150 አውሮፕላኖች ያሉት ሲሆን የበረራ ተደራሽነቱንና ጥራቱን ይበልጥ ለማሳደግ 117 አዳዲስ አውሮፕላኖችን ለመግዛት በሂደት ላይ መሆኑን ጠቁመዋል።

ያለፉት ሰማንያ ዓመታት ለአየር መንገዱ የታታሪነት፣ የጠንክሮ መስራት እና የስኬት ዘመናት መሆናቸውን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የገጠሙትን ፈተናዎች በጽናት በማለፍ አፍሪካን ከዓለም ጋር የሚያገናኝ ቀዳሚ የአቪዬሽን ተቋም መሆኑን በተግባር ማረጋገጡን ጠቅሰዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026