የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

ለትንሳኤ በዓል በቂ ምርት ወደ ገበያ በመቅረቡ በተረጋጋ ሁኔታ እየተገበያየን ነው - የሚዛን አማን ከተማ ነዋሪዎች

Apr 12, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሚዛን አማን፣ ሚያዝያ 3/2018 (ኢዜአ) ፡-ለትንሳኤ በዓል በቂ ምርት ወደ ገበያ በመቅረቡ ተረጋግተው እየተገበያዩ መሆኑን የሚዛን አማን ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ።

ነዋሪዎቹ አቅማቸው በፈቀደው መልኩ በመሸመት በዓሉን ከጎረቤቶቻቸው ጋር በደስታ ለማክበር መዘጋጀታቸውንም ገልጸዋል።

አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የሚዛን አማን ከተማ ነዋሪዎች ለትንሳኤ በዓል በቂ ምርት ወደ ገበያ በመቅረቡ በተረጋጋ ሁኔታ እየተገበያዩ መሆኑን ገልጸዋል፡፡


ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል ወይዘሮ ጨነቁ በፍቃዱ በምርቶች ላይ የተወሰነ የዋጋ ጭማሪ ቢኖርም ሁሉንም ምርቶች በተለያየ ዋጋና መጠን አማራጭ እያገኘን ነው ብለዋል።

ከነዳጅ እጥረት ጋር ተያይዞ በተለይ የፋብሪካ ውጤቶችና ከሌላ አካባቢ የሚጫኑ የፍጆታ ምርቶች እጥረት ይከሰታል የሚል ስጋት እንደነበረባቸው ገልጸው ለምርት አቅርቦት መንግሥት በሰጠው ትኩረት ምንም እጥረት አለመከሰቱን ተናግረዋል።

በመንግሥት የሚደረገው የዋጋ ቁጥጥርና የምርት ክትትል በሌሎችም ጊዜያት ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባም አመልክተዋል።


ወይዘሮ ባንቻለም አሉላ የተባሉ ሌላዋ የሚዛን አማን ከተማ ነዋሪ በበኩላቸው የተሻለ የበዓል ዋዜማ ድባብ ገበያ ላይ መኖሩን ገልጸዋል።

ቀይና ነጭ ሽንኩርት በተመጣጣኝ ዋጋ መሸመታቸውን ገልጸው በተለይ የሰንበት ገበያ ላይ ምርት በስፋት መቅረቡ የግብይት አማራጩን እንዳሰፋ ነው የተናገሩት።

የእርድ እንስሳት ዋጋ ጭማሪ ቢኖርም አቅማቸው የሚፈቅደውን መርጠው እየሸመቱ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ መምህር አየለ ደሳለኝ የተባሉ የከተማዋ ነዋሪ ናቸው።


የእርድ እንስሳት መጠነኛ ጭማሪ ማሳየታቸውን ገልጸው በገበያው ግን በግ እና ዶሮ እንደልብ በመቅረባቸው በአማራጭ እየተገበያዩ መሆኑን ገልጸዋል።

የቤንች ሸኮ ዞን ንግድ እና ኢንቨስትመንት መምሪያ የሸማች ዘርፍ ባለሙያ አቶ አፈራ አያሌው ለዘንድሮ የፋሲካ በዓል ጠንካራ የገበያ ትስስር በመፍጠር ምርት ለገበያ እንዲቀርብ መደረጉን ገልጸዋል።


የፋብሪካ ውጤቶችን ከጅምላ ነጋዴዎች ጋር በመነጋገር በሰንበት ገበያ ላይ በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያገበያዩ ማድረግ መቻሉን አመልክተዋል።

ሕገ ወጥነትን ለመከላከል እየተደረገ ባለው ጠንካራ ክትትል ያለ አግባብ በሚንቀሳቀሱ ነጋዴዎች ላይ እርምጃ በመውሰድ የበዓል ገበያውን የተረጋጋ ማድረግ መቻሉን ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026