🔇Unmute
ቢሾፍቱ፤ ሚያዚያ 7 /2018 (ኢዜአ)፦ የኦሮሚያ ክልል መንግስት ግልጽ ዕቅድ በማስቀመጥ የሕዝቡን ሕይወት የሚቀይሩ የልማት ሥራዎችን እያከናወነ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ ተናገሩ።
የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት እና የፓርቲ የሦስተኛ ሩብ ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ በቢሾፍቱ ከተማ መካሄድ ጀምሯል።
በግምገማ መድረኩ ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ እና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ሰዓዳ አብዱራህማን፣ በብልጽግና ፓርቲ የኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ከፍያለው ተፈራ እና ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ በዚሁ ወቅት፤ ባለፉት ዓመታት የክልሉ መንግስት ግልጽ ዕቅድ በማስቀመጥ የሕዝቡን ሕይወት የሚቀይሩ የልማት ሥራዎችን እያከናወነ ነው ብለዋል።
በተለይም በሁሉም ዘርፎች በኢኒሼቲቭ መልክ ሲተገበሩ የቆዩ የልማት ስራዎች በክልሉ መሰረታዊ ለውጦች እንዲመዘገቡ ያስቻሉ መሆናቸውን አንስተዋል።

በመድረኩ ላይ ባለፉት ዘጠኝ ወራት የተከናወኑ የመንግስት እና የፓርቲ የሥራ አፈጻጸም ሪፖርቶች ቀርበው፣ የታዩ ጥንካሬዎችና ድክመቶች ተለይተው ለቀጣይ ሥራዎች አቅጣጫ ይቀመጣልም ተብሏል።
በተጨማሪም የ2019 ዓ.ም የዕቅድ መነሻ የሚቀርብ ሲሆን፣ በግምገማው ላይ የዞን፣ የከተማ እና የወረዳ አመራሮች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025
ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...
Feb 8, 2025