የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የክልሉ መንግስት የሕዝቡን ሕይወት የሚቀይሩ የልማት ሥራዎችን እያከናወነ ነው- ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ

Apr 15, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ቢሾፍቱ፤ ሚያዚያ 7 /2018 (ኢዜአ)፦ የኦሮሚያ ክልል መንግስት ግልጽ ዕቅድ በማስቀመጥ የሕዝቡን ሕይወት የሚቀይሩ የልማት ሥራዎችን እያከናወነ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ ተናገሩ።

የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት እና የፓርቲ የሦስተኛ ሩብ ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ በቢሾፍቱ ከተማ መካሄድ ጀምሯል።

በግምገማ መድረኩ ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ እና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ሰዓዳ አብዱራህማን፣ በብልጽግና ፓርቲ የኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ከፍያለው ተፈራ እና ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።


ርዕሰ መስተዳድሩ በዚሁ ወቅት፤ ባለፉት ዓመታት የክልሉ መንግስት ግልጽ ዕቅድ በማስቀመጥ የሕዝቡን ሕይወት የሚቀይሩ የልማት ሥራዎችን እያከናወነ ነው ብለዋል።

በተለይም በሁሉም ዘርፎች በኢኒሼቲቭ መልክ ሲተገበሩ የቆዩ የልማት ስራዎች በክልሉ መሰረታዊ ለውጦች እንዲመዘገቡ ያስቻሉ መሆናቸውን አንስተዋል።


በመድረኩ ላይ ባለፉት ዘጠኝ ወራት የተከናወኑ የመንግስት እና የፓርቲ የሥራ አፈጻጸም ሪፖርቶች ቀርበው፣ የታዩ ጥንካሬዎችና ድክመቶች ተለይተው ለቀጣይ ሥራዎች አቅጣጫ ይቀመጣልም ተብሏል።

በተጨማሪም የ2019 ዓ.ም የዕቅድ መነሻ የሚቀርብ ሲሆን፣ በግምገማው ላይ የዞን፣ የከተማ እና የወረዳ አመራሮች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሚያዝያ እና ግንቦት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት ከምስል ጋር!

  የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...

Jun 4, 2026

በዲጂታል ክህሎት ራሳችንን እያበቃን ነው - ተማሪዎች

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...

Jun 1, 2026

በኦሮሚያ ክልል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ የአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት ተሰጥቷል

አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...

May 25, 2026

በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው

ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...

May 15, 2026