🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 7/2018 (ኢዜአ)፦የአዲስ አበባ ከተማ ትንሣኤ የአፍሪካ ከተሞችን ሥልጣኔና ዕድገት ለማፋጠን አዲስ ተስፋን የፈነጠቀ መሆኑን የአፍሪካ አደጋ ስጋት አቅም አባል ሀገራት ጉባዔ ተሳታፊዎች ገለጹ።
የአፍሪካ አደጋ ስጋት አቅም አባል ሀገራት ጉባዔ ተሳታፊዎች የአዲስ አበባን የልማት ሥራዎች በጎበኙበት ወቅት የጅቡቲ፣ የሱዳን እና የዛምቢያ ልዑክ አባላት ሀሳባቸውን ለኢዜአ አጋርተዋል።
ከአሥር ዓመታት በፊት መዲናዋን የጎበኙትና ከጅቡቲ የመጡት ኢሳም አብዱልሃኪም፤ ያኔ በአዕምሯቸው የተቀረጸው የአዲስ አበባ ደብዛዛና ጎስቋላ ገፅታ ዛሬ ላይ ተቀይሮ ማየታቸውን በአግራሞት አስታውሰዋል።

በአሁኑ ወቅት በመዲናዋ በበአጭር ጊዜ የተከናወኑት አስደናቂ የልማት ሥራዎች አዲስ አበባን ለነዋሪዎቿ ምቹ ለጎብኝዎቿ ደግሞ ማራኪ እንድትሆን አድርጓል ብለዋል።
በተለይም የኮሪደርና የወንዝ ዳርቻ የልማቱ የመዲናዋን የኢኮኖሚ አቅም ከማሳደጋቸውም ባሻገር ዓለም አቀፍ የከተሜነት የውድድር መስፈርቶችን እንድታሟላ እንዳስቻላት ገልጸዋል።
በአጭር ጊዜ ውስጥ በጥራትና በፈጣን ልማት የተመዘገቡ ውጤቶች አዲስ አበባን በጽዳታቸውና ውበታቸው ከሚጠቀሱ የዓለም ታላላቅ ከተሞች ተርታ እንድትሰለፍ እንዳደረጋት ተናግረዋል።
በቆይታቸው ወቅት ከነዋሪዎች የተቸራቸው የከበረ የእንግዳ ተቀባይነት መንፈስም የኢትዮጵያውያንን ጥልቅ ትብብርና በጎነት በሚገባ የተመለከቱበት አጋጣሚ መሆኑን አንስተዋል።
ከሱዳን የመጡት እስማዔል አሊ በበኩላቸው፤ የአዲስ አበባ አስደናቂ የለውጥ ጉዞ የአፍሪካ ከተሞችን ወደላቀ ምዕራፍ ለማሸጋገር ትልቅ ትምህርትና ተሞክሮ እንደሚሆን ገልጸዋል።

በአሁኑ ወቅትም አዲስ አበባ በአፍሪካ ስሉጥ ከሆኑ ዘመናዊ የከተማ ፈርጦች መካከል መሰለፏን በጉብኝታቸው እንደታዘቡ ተናግረዋል።
በመዲናዋ ቆይታቸውም በኢኮኖሚና ኢንቨስትመንት ዘርፍ የተመዘገበው እመርታ ከተማዋ በዕድገት ጎዳና እየገሰገሰች መሆኗን እንዳረጋገጡ አንስተዋል።
ከዛምቢያ የመጡት መሲ ችሉ፤ የአዲስ አበባ አስደናቂ የልማት ስኬት በራስ አቅምና ቀለም መገንባቱ ዘርፈ ብዙ ትርጉም የሚሰጠው የመቻል ውጤት ነው ብለዋል።

ይህም ለአፍሪካዊያን ያለአንዳች እርዳታና ጥገኝነት የላቁና የሰለጠኑ ከተሞችን መገንባት እንደሚቻል ትምህርት እንደሚሰጥ አስረድተዋል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026