የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የመዲናዋ ትንሣኤ የአፍሪካ ከተሞችን ሥልጣኔና ዕድገት ለማፋጠን አዲስ ተስፋን የፈነጠቀ ነው

Apr 16, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 7/2018 (ኢዜአ)፦የአዲስ አበባ ከተማ ትንሣኤ የአፍሪካ ከተሞችን ሥልጣኔና ዕድገት ለማፋጠን አዲስ ተስፋን የፈነጠቀ መሆኑን የአፍሪካ አደጋ ስጋት አቅም አባል ሀገራት ጉባዔ ተሳታፊዎች ገለጹ።

የአፍሪካ አደጋ ስጋት አቅም አባል ሀገራት ጉባዔ ተሳታፊዎች የአዲስ አበባን የልማት ሥራዎች በጎበኙበት ወቅት የጅቡቲ፣ የሱዳን እና የዛምቢያ ልዑክ አባላት ሀሳባቸውን ለኢዜአ አጋርተዋል።

ከአሥር ዓመታት በፊት መዲናዋን የጎበኙትና ከጅቡቲ የመጡት ኢሳም አብዱልሃኪም፤ ያኔ በአዕምሯቸው የተቀረጸው የአዲስ አበባ ደብዛዛና ጎስቋላ ገፅታ ዛሬ ላይ ተቀይሮ ማየታቸውን በአግራሞት አስታውሰዋል።


በአሁኑ ወቅት በመዲናዋ በበአጭር ጊዜ የተከናወኑት አስደናቂ የልማት ሥራዎች አዲስ አበባን ለነዋሪዎቿ ምቹ ለጎብኝዎቿ ደግሞ ማራኪ እንድትሆን አድርጓል ብለዋል።

በተለይም የኮሪደርና የወንዝ ዳርቻ የልማቱ የመዲናዋን የኢኮኖሚ አቅም ከማሳደጋቸውም ባሻገር ዓለም አቀፍ የከተሜነት የውድድር መስፈርቶችን እንድታሟላ እንዳስቻላት ገልጸዋል።

በአጭር ጊዜ ውስጥ በጥራትና በፈጣን ልማት የተመዘገቡ ውጤቶች አዲስ አበባን በጽዳታቸውና ውበታቸው ከሚጠቀሱ የዓለም ታላላቅ ከተሞች ተርታ እንድትሰለፍ እንዳደረጋት ተናግረዋል።

በቆይታቸው ወቅት ከነዋሪዎች የተቸራቸው የከበረ የእንግዳ ተቀባይነት መንፈስም የኢትዮጵያውያንን ጥልቅ ትብብርና በጎነት በሚገባ የተመለከቱበት አጋጣሚ መሆኑን አንስተዋል።

ከሱዳን የመጡት እስማዔል አሊ በበኩላቸው፤ የአዲስ አበባ አስደናቂ የለውጥ ጉዞ የአፍሪካ ከተሞችን ወደላቀ ምዕራፍ ለማሸጋገር ትልቅ ትምህርትና ተሞክሮ እንደሚሆን ገልጸዋል።


በአሁኑ ወቅትም አዲስ አበባ በአፍሪካ ስሉጥ ከሆኑ ዘመናዊ የከተማ ፈርጦች መካከል መሰለፏን በጉብኝታቸው እንደታዘቡ ተናግረዋል።

በመዲናዋ ቆይታቸውም በኢኮኖሚና ኢንቨስትመንት ዘርፍ የተመዘገበው እመርታ ከተማዋ በዕድገት ጎዳና እየገሰገሰች መሆኗን እንዳረጋገጡ አንስተዋል።

ከዛምቢያ የመጡት መሲ ችሉ፤ የአዲስ አበባ አስደናቂ የልማት ስኬት በራስ አቅምና ቀለም መገንባቱ ዘርፈ ብዙ ትርጉም የሚሰጠው የመቻል ውጤት ነው ብለዋል።


ይህም ለአፍሪካዊያን ያለአንዳች እርዳታና ጥገኝነት የላቁና የሰለጠኑ ከተሞችን መገንባት እንደሚቻል ትምህርት እንደሚሰጥ አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሚያዝያ እና ግንቦት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት ከምስል ጋር!

  የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...

Jun 4, 2026

በዲጂታል ክህሎት ራሳችንን እያበቃን ነው - ተማሪዎች

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...

Jun 1, 2026

በኦሮሚያ ክልል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ የአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት ተሰጥቷል

አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...

May 25, 2026

በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው

ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...

May 15, 2026