🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 7/2018 (ኢዜአ)፦የአዲስ አበባ ከተማ ትንሣኤ የአፍሪካ ከተሞችን ሥልጣኔና ዕድገት ለማፋጠን አዲስ ተስፋን የፈነጠቀ መሆኑን የአፍሪካ አደጋ ስጋት አቅም አባል ሀገራት ጉባዔ ተሳታፊዎች ገለጹ።
የአፍሪካ አደጋ ስጋት አቅም አባል ሀገራት ጉባዔ ተሳታፊዎች የአዲስ አበባን የልማት ሥራዎች በጎበኙበት ወቅት የጅቡቲ፣ የሱዳን እና የዛምቢያ ልዑክ አባላት ሀሳባቸውን ለኢዜአ አጋርተዋል።
ከአሥር ዓመታት በፊት መዲናዋን የጎበኙትና ከጅቡቲ የመጡት ኢሳም አብዱልሃኪም፤ ያኔ በአዕምሯቸው የተቀረጸው የአዲስ አበባ ደብዛዛና ጎስቋላ ገፅታ ዛሬ ላይ ተቀይሮ ማየታቸውን በአግራሞት አስታውሰዋል።

በአሁኑ ወቅት በመዲናዋ በበአጭር ጊዜ የተከናወኑት አስደናቂ የልማት ሥራዎች አዲስ አበባን ለነዋሪዎቿ ምቹ ለጎብኝዎቿ ደግሞ ማራኪ እንድትሆን አድርጓል ብለዋል።
በተለይም የኮሪደርና የወንዝ ዳርቻ የልማቱ የመዲናዋን የኢኮኖሚ አቅም ከማሳደጋቸውም ባሻገር ዓለም አቀፍ የከተሜነት የውድድር መስፈርቶችን እንድታሟላ እንዳስቻላት ገልጸዋል።
በአጭር ጊዜ ውስጥ በጥራትና በፈጣን ልማት የተመዘገቡ ውጤቶች አዲስ አበባን በጽዳታቸውና ውበታቸው ከሚጠቀሱ የዓለም ታላላቅ ከተሞች ተርታ እንድትሰለፍ እንዳደረጋት ተናግረዋል።
በቆይታቸው ወቅት ከነዋሪዎች የተቸራቸው የከበረ የእንግዳ ተቀባይነት መንፈስም የኢትዮጵያውያንን ጥልቅ ትብብርና በጎነት በሚገባ የተመለከቱበት አጋጣሚ መሆኑን አንስተዋል።
ከሱዳን የመጡት እስማዔል አሊ በበኩላቸው፤ የአዲስ አበባ አስደናቂ የለውጥ ጉዞ የአፍሪካ ከተሞችን ወደላቀ ምዕራፍ ለማሸጋገር ትልቅ ትምህርትና ተሞክሮ እንደሚሆን ገልጸዋል።

በአሁኑ ወቅትም አዲስ አበባ በአፍሪካ ስሉጥ ከሆኑ ዘመናዊ የከተማ ፈርጦች መካከል መሰለፏን በጉብኝታቸው እንደታዘቡ ተናግረዋል።
በመዲናዋ ቆይታቸውም በኢኮኖሚና ኢንቨስትመንት ዘርፍ የተመዘገበው እመርታ ከተማዋ በዕድገት ጎዳና እየገሰገሰች መሆኗን እንዳረጋገጡ አንስተዋል።
ከዛምቢያ የመጡት መሲ ችሉ፤ የአዲስ አበባ አስደናቂ የልማት ስኬት በራስ አቅምና ቀለም መገንባቱ ዘርፈ ብዙ ትርጉም የሚሰጠው የመቻል ውጤት ነው ብለዋል።

ይህም ለአፍሪካዊያን ያለአንዳች እርዳታና ጥገኝነት የላቁና የሰለጠኑ ከተሞችን መገንባት እንደሚቻል ትምህርት እንደሚሰጥ አስረድተዋል።
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025