የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ እንዲሳካ ዜጎች በያሉበት የሚያደርጉትን አስተዋጽኦ ሊያጠናክሩ ይገባል - ምሁራን

Apr 16, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሚዛን አማን፣ ሚያዝያ 8/2018 (ኢዜአ)- የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ እንዲሳካ ዜጎች ዓለም አቀፍ ሕግና ሥርዓትን በጠበቀ መንገድ የሚያደርጉትን አስተዋጽኦ ሊያጠናክሩ ይገባል ሲሉ ምሁራን ገለጹ።

የቀጣናው ሀገራትም ከሌሎች ጫና በመላቀቅ የመተባበር እና በሰጥቶ መቀበል መርህ አብሮ የመልማት አማራጭን ሊተገበሩ እንደሚገባ ተመላክቷል።

ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉ የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ ከግብ እንዲደርስ ዜጎች በያሉበት ዓለም አቀፍ ሕግና ሥርዓትን በጠበቀ መንገድ የሚያደርጉትን አስተዋጽኦ ማጠናከር አለባቸው፡፡

በዩኒቨርሲቲው የፖለቲካል ሳይንስ መምህር ቢመርቅ በሪሁን እንዳሉት ለኢትዮጵያ የባሕር በር ጉዳይ የቅንጦት ሳይሆን የሕልውና ጉዳይ መሆኑን ሁሉም በሚገባ ሊያውቀው ይገባል።

የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ያለው ብሔራዊ ጉዳይ በመሆኑ ከግብ እንዲደርስ የዜጎች ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን ገልጸው፤ በያሉበት ዓለም አቀፍ ሕግና ሥርዓትን በጠበቀ መንገድ አስተዋጿቸውን ሊያጠናክሩ ይገባል ብለዋል።

"እንደሀገር ባጋጠመ የፖለቲካ ስብራት ከባህር በር ተነጥለን ቆይተናል፤ ይህ ስህተት ነው" ያሉት መምህሩ፣ ስህተቱን ሰላማዊና ዲፕሎማሲያዊ በሆነ መንገድ ለማረም የተጀመረውን እንቅስቃሴ ሁሉም በቁርጠኝነት መደገፍ አለበት ብለዋል።

ዓለም አቀፍ ሕጎችና ሥርአቶች በሚፈቅዱት የድርድርና የሰጥቶ መቀበል መርህ መሰረት የወደብ ባለቤትነት ታሪክን ዳግም ለማደስ የሚያስችል የትውልድ እንቅስቃሴ ላይ መድረሱ ትልቅ ሀገራዊ ለውጥ መሆኑንም አንስተዋል።

እንደ መምህር ቢመርቅ ገለጻ የሀገራት ሉዓላዊነት በተጠበቀ መልኩ ሌሎች ሀገራትም የባሕር በር የማግኘት መብት ስላላቸው የቀጣናው ሀገራት ትብብርን ከጋራ ተጠቃሚነት ጋር በማስተሳሳር ሊያዩት ይገባል።

ለዚህም ፖለቲከኞች፣ ዳያስፖራው፣ ምሁራን እና ሌሎችም ዜጎች በያሉበት የሚያደርጉትን ዘርፈ ብዙ ዲፕሎማሲያዊ ጥረቶች አጠናክረው መንቀሳቀስ አለባቸው ብለዋል።

"ማንም ዜጋ ለሀገር ብሔራዊ ጥቅም ቅድሚያ ሰጥቶ የመሥራትና የመታገል ኃላፊነት አለበት" ያሉት ደግሞ በዩኒቨርሲቲው የሥነ ዜጋና ሥነ ምግባር መምህር ሙሉቀን አየለ ናቸው።

ሀገር በዜጎች ድምር ጥረት ጥቅሟን ማስጠበቅና ከፍ ማለት እንደምትችል ገልጸው፣ የዛሬው ትውልድ አጀንዳ ለሆነው የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ገለልተኛ ሊሆን እንደማይችል አንስተዋል።

በመሆኑም የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄው ከግብ እንዲደርስ ሁሉም ያለቅድመ ሁኔታ አስፈላጊውን ጥረት ማድረግ አለበት ብለዋል።

እንደ ዩኒቨርሲቲ መምህርነታቸው ለጉዳዩ ይጠቅማሉ የሚሏቸውን ሀሳቦች በማቅረብና አስቻይ መንገዶችን በማመላከት ኃላፊነታቸውን እንደሚወጡም አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ ነው -ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚው ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለአፍሪካ አገራት ትልቅ አርአያ ናቸው - የላይቤሪያ ልዑካን ቡድን

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...

Apr 16, 2026

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026

<p>ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በቦንጋ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው</p>

ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...

Feb 24, 2025