የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂን ግብ ለማሳካት የዲጂታል አስተሳሰብ ለውጥ ያስፈልጋል

Apr 17, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 8 /2018 (ኢዜአ)፦የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂን ግብ ለማሳካት የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ክህሎትና የዲጂታል አስተሳሰብ ለውጥ እንደሚያስፈልግ የኢትዮጵያ ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ፓርክ ዋና ሥራ አስፈፃሚ በለጠ እሱባለው ገለጹ፡፡

የኢትዮጵያ ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ፓርክ ከአፍሪካ ዲጂታልና ኢኖቬሽን ቴክኖሎጂ አካዳሚ ጋር በመተባበር "አመራር በሰው ሰራሽ አስተውሎት" በሚል መሪ ሃሳብ ሴሚናር አዘጋጅቷል፡፡


የኢትዮጵያ ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ፓርክ ዋና ሥራ አስፈፃሚ በለጠ እሱባለው በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂን መገልገል ምርጫ ሳይሆን ግዴታ ሆኗል፡፡

ዘመኑ የሚጠይቀውን አመራር ለመስጠት በዘርፉ ራስን ማዘጋጀት እንደሚገባ ገልጸው፤ እንደ ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ፓርክ ያሉ ተቋማት ደግሞ ሥራቸው ከሰው ሰራሽ አስተውሎት ጋር የተያያዘ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በዚህም ፓርኩ በዘርፉ ልምድና አቅም ያላቸው ባለሙያዎችን በማምጣት የተቋሙን ሰራተኞችና የሥራ ሀላፊዎች ሰው ሰራሽ አስተውሎትን እንዴት መጠቀም እንዳለባቸው ግንዛቤ እንዲፈጠርላቸው እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ውጤታማ ሥራዎችን በማከናወን የተቋሙን ግብ ለማሳካት የሰው ሰራሽ አስተውሎትን መሰረት ያደረገ ጥረት መኖሩንም ተናግረዋል፡፡

የዲጂታል ኢትዮጵያን 2030 ስትራቴጂ ግብ ለማሳካት የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ክህሎትና የዲጂታል አስተሳሰብ ለውጥ ማምጣት ይገባል ብለዋል፡፡

የአፍሪካ ዲጂታልና ኢኖቬሽን ቴክኖሎጂ አካዳሚ ቦርድ ሊቀ መንበርና የአፍሪካ ቴክኖሎጂ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ባህሩ ዘይኑ፤ ሰው ሰራሽ አስተውሎት በማህበራዊ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ዘርፎች ጉልህ ሚና እንዳለው ገልጸዋል፡፡


ኢትዮጵያ ሰው ሰራሽ አስተውሎት ያለውን ዓለም አቀፋዊ ተጽዕኖ በመረዳት የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት አቋቁማለች ብለዋል፡፡

ከዚህም ባለፈ በአፍሪካ ቀዳሚ የሆነው የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ /ኤ.አይ/ ዩኒቨርሲቲ ለመክፈት በሂደት ላይ መሆኗን አስታውሰዋል፡፡

ኢትዮጵያ የቴክኖሎጂ ገዥና ተቀባይ እንደነበረች አስታውሰው፤ ፖሊሲ በማዘጋጀት የቴክኖሎጂ መሰረተ ልማት በመዘርጋት ቴክኖሎጂ ሰጭና ለሌሎች ሀገራት አቅራቢ ወደ መሆን ደረጃ ተሸጋግራለች ብለዋል፡፡

የአፍሪካ ዲጂታልና ኢኖቬሽን ቴክኖሎጂ አካዳሚ ተባባሪ መስራችና ዋና ሥራ አስፈፃሚ ፕሮፌሰር ሸጋው አናጋው፤ ሰው ሰራሽ አስተውሎት በሁሉም ዘርፎች ለውጥ እያመጣ መሆኑን ተናግረዋል፡፡


ሰው ሰራሽ አስተውሎት የአሰራር ለውጥ መፍጠሩን የጠቀሱት ፕሮፌሰር ሸጋው፤ የተቋማት መሪዎች በቀደመው መንገድ መምራት አይችሉም ብለዋል፡፡

አርቴፊሻል ኢንተለጀንስን ውጤት በሚያመጣ መንገድ ለመጠቀም የተቋማት መሪዎችን በቴክኖሎጂ ማብቃት እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡

በኢትዮጵያ የዲጂታል ሽግግር ለማምጣት የአስተሳሰብና የባህል ለውጥ እንደሚያስፈልግ ገልጸው፤ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ዕውቀትና ክህሎት ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል፡፡

የሰው ሰራሽ አስተውሎት ዘመን ሁኔታዎችን አስቀድሞ በመተንበይ ለውጥ በሚያመጡ ጉዳዮች ላይ አመራር ለመስጠት ክህሎት፣ ሥነ ምግባርና ሽግግር መፍጠር ይገባል ብለዋል፡፡


በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የኢኖቬሽን ልማት መሪ ሥራ አስፈጻሚ ሰላምይሁን አደፍርስ በበኩላቸው፤ ሰው ሰራሽ አስተውሎት የመሪነት ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ለዚህ ደግሞ መንግሥት የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ፖሊሲ በማውጣት ዘርፉን ለማሳደግ በትኩረት እየሰራ ነው ብለዋል፡፡

ሰው ሰራሽ አስተውሎት በፍጥነት እያደገ ያለ ዘርፍ መሆኑን ጠቅሰው፤ የዘርፉን እድገት የሚመጥን የመንግስት ቁርጠኝነት መኖሩን ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ ነው -ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚው ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለአፍሪካ አገራት ትልቅ አርአያ ናቸው - የላይቤሪያ ልዑካን ቡድን

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...

Apr 16, 2026

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026

<p>ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በቦንጋ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው</p>

ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...

Feb 24, 2025