የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የዓለም ባንክ እና ጣልያን ለኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሪፎርም ድጋፋቸውን እንደሚያጠናክሩ ገለጹ

Apr 17, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 8/2018 (ኢዜአ)፦ የዓለም ባንክ እና ጣልያን ለኢትዮጵያ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም ድጋፍ ማድረጋቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስታወቁ።

በገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ የተመራ የኢትዮጵያ ልዑክ፣ የሶስትዮሽ አጋርነትን ይበልጥ ለማሳደግ ያለመ ከፍተኛ ምክክር ከዓለም ባንክ እና ከጣልያን ልዑካን ቡድን ጋር አካሂዷል።

የውይይቱ ዋነኛ ትኩረት የኢትዮጵያን ቀጣይ የኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮግራም ለመደገፍ በሦስቱ ወገኖች መካከል ያለውን ትብብር ማጠናከር ነው።

ሀገሪቱ ቅድሚያ ከምትሰጣቸው የልማት ጉዳዮች ጋር የተጣጣመ፣ ወቅቱን የጠበቀና አስተማማኝ የፋይናንስ ድጋፍ ማሰባሰብ በሚቻልባቸው መንገዶች ላይም መክረዋል።


የኢትዮጵያ ልዑክ በቅርቡ የተመዘገቡ የማክሮ ኢኮኖሚ ስኬቶችን ያብራራ ሲሆን፤ መንግሥት የጀመረውን የማሻሻያ እንቅስቃሴ ለማስቀጠል፣ የፋይናንስ ሥርዓትን (Fiscal Discipline) ይበልጥ ለማስጥበቅና ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ ዕድገትን ለማረጋገጥ ያለውን ጽኑ አቋም በድጋሚ አረጋግጧል።

በውይይቱ የልማት አጋሮች የሚያደርጉት ድጋፍ የተቀናጀ መሆን ያለው ጠቀሜታ አጽንኦት ተሰጥቶበታል።

ይህም የሚደረገው ድጋፍ የሚፈለገውን ውጤት እንዲያመጣና የሀብት አጠቃቀም ውጤታማ እንዲሆን የሚያስችል እንደሆነ ተመላክቷል።

የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያውን ከማገዝ ባለፈ፣ ኢትዮጵያ ተለዋዋጭና ውስብስብ የሆነውን የዓለም አቀፍ የኢኮኖሚ ሁኔታ ተቋቁማ እንድትሻገር የሚያስችሉ የተቀናጁ የድጋፍ ማዕቀፎች ላይ ውይይት ተካሂዷል።

የጣልያን ልዑክ በበኩሉ ኢትዮጵያ ለምታደርገው የልማት ጥረት ያለውን አጋርነት በድጋሚ ያረጋገጠ ሲሆን፣ በተለይም በሁለትዮሽ ትብብር እና ከዓለም አቀፍ የፋይናንስ ማዕቀፎች ጋር በተጣጣመ መልኩ ድጋፉን እንደሚያጠናክር ገልጿል።

በተመሳሳይ ዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮግራም ቀጣይነት ስላለው ድጋፍ በመግለጽ፣ ውጤታማ የፋይናንስ ትብብርን ለማሳደግ ከአጋሮች ጋር በቅርበት ለመሥራት ዝግጁ መሆኑን አሳውቋል።

ወቅታዊ የኢኮኖሚ ተግዳሮቶችንና የፋይናንስ ውስንነቶችን በዘላቂነት ለመወጣት ጽኑ አጋርነትና የጋራ ጥረት አስፈላጊ መሆኑንም በውይይታቸው አጽንኦት ሰጥተዋል።


ከዚህም ባሻገር ተጨባጭ የልማት ውጤቶችን ለማስመዝገብ ዘላቂ የፖሊሲ ቅንጅት፣ የተቀናጀ ተግባቦት እና የጋራ ተጠያቂነት አስፈላጊ መሆናቸው በውይይቱ ወቅት ተመልክቷል።

በሦስቱ ወገኖች መካከል ያለውን ጥምረት ይበልጥ ለማጠናከርና የተቀናጀ የትብብር ማዕቀፍን ለማዘጋጀት የሚደረገውን ጥረት ለማሳለጥ በውይይቱ የጋራ ስምምነት ላይ ተደርሷል።

ኢትዮጵያ ለረጅም ጊዜ የሚዘልቅ የኢኮኖሚ ጥንካሬና ዕድገትን ለማረጋገጥ ወሳኝ የሆኑ መዋቅራዊ ማሻሻያዎችን ተግባራዊ ለማድረግ ያላትን ጽኑ አቋም በድጋሚ ማረጋገጧን የገንዘብ ሚኒስቴር ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሚያዝያ እና ግንቦት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት ከምስል ጋር!

  የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...

Jun 4, 2026

በዲጂታል ክህሎት ራሳችንን እያበቃን ነው - ተማሪዎች

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...

Jun 1, 2026

በኦሮሚያ ክልል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ የአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት ተሰጥቷል

አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...

May 25, 2026

በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው

ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...

May 15, 2026