የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የታዳሽ ኃይል የልማት ስኬቶች የአካባቢ ደኅንነት ጥበቃ የድል ማሕተሞች ናቸው 

Apr 17, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 8 /2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ የታዳሽ ኃይል የልማት ስኬቶች የአካባቢ ደኅንነት ጥበቃን በማረጋገጥ የብልፅግናን ጉዞ የሚያፋጥኑ የድል ማሕተሞች መሆናቸውን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ስራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን ሄጦሳ ወረዳ ኢተያ አካባቢ የተገነባውን የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በዛሬው ዕለት መርቀው ሥራ አስጀምረዋል።


የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በዚሁ ወቅት፣ ኢትዮጵያ ከውሃ፣ ከንፋስ፣ ከፀሐይ፣ ከጂኦተርማል እንዲሁም ከባዮ ጋዝና ታዳሽ ኃይል አማራጮች እምቅ አቅም እንዳላት ገልጸዋል።

በዚህም እያደገ የመጣውን የኃይል ፍላጎት አስተማማኝና ቀጣይነት ባለው መልኩ ለመመለስ የሚያስችሉ ተግባራት እየተሰሩ መሆናቸውን አመላክተዋል።

ዛሬ የተመረቀው የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ የዚሁ አካል መሆኑን አንስተው፤ ፕሮጅክቱ በ29 ተርባይኖች 100 ሜጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም ያለው ነው ብለዋል።

ይህም ሀገሪቱ ከንፋስ ኃይል የምታገኘውን የማመንጨት አቅም ወደ 504 ሜጋ ዋት በማሳደግ ተቋሙ የኃይል ስብጥርን ለማመጣጠን የሰጠውን ትኩረት የሚያግዝ ነው ብለዋል፡፡


የፕሮጀክቱ ወደ ስራ መግባት ተደማሪ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር የሚያስችል መሆኑን በመግለጽ፤ የኢትዮጵያ የታዳሽ ኃይል የልማት ስኬቶች የአካባቢ ደኅንነት ጥበቃን በማፋጠን የብልፅግናን ጉዞ የሚያፋጥኑ የድል ማሕተሞች መሆናቸውን ገልጸዋል።

በኢትዮጵያ የዴንማርክ አምባሳደር ሱን ክሮግስትራፕ በበከላቸው እንደገለጹት፤ የንፋስ ኃይል ማመንጫው ለዘላቂ ኢኮኖሚ እድገትና የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል ወሳኝ ነው፡፡


ኢትዮጵያና ዴንማርክ በዚህ ረገድ በጋራ እየሰሩ መሆኑን አንስተው፤ የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ይህን የሚያጠናክር ከመሆኑም ባለፈ ለቀጣይ ታዳሽ ኃይል ኢንቨስትመንት መሰረት የሚጥል መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በተለይም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ( ዶ/ር) አነሳሸነት የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር ለዓለም አርአያ የሆነ ተግባር መሆኑን አንስተዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ ነው -ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚው ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለአፍሪካ አገራት ትልቅ አርአያ ናቸው - የላይቤሪያ ልዑካን ቡድን

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...

Apr 16, 2026

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026

<p>ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በቦንጋ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው</p>

ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...

Feb 24, 2025