የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ገቢን አሟጦ ለመሰብሰብ በተደረገ ጥረት አበረታች ውጤት ተመዝግቧል 

Apr 17, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሆሳዕና፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ባለፉት ዘጠኝ ወራት ገቢን አሟጦ ለመሰብሰብ በተደረገ ጥረት አበረታች ውጤት መመዝገቡን የክልሉ ገቢዎች ቢሮ አስታወቀ፡፡

በክልሉ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ18 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ መቻሉም ተመላክቷል።

የቢሮው ኃላፊ ቀመሪያ ረሻድ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በክልሉ በህዝብ ለሚነሱ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ፈጣን ምላሽ ለመስጠት ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ በአግባቡ መሰብሰብ ያስፈልጋል።

በክልሉ በተያዘው በጀት ዓመት ከመደበኛና ከማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ከ27 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደ ተግባር መገባቱን አመልክተዋል።

በዚህም ባለፉት ዘጠኝ ወራት ገቢን አሟጦ ለመሰብሰብ በተደረገ ጥረት ከ18 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ በመሰብሰብ አበረታች ውጤት መመዝገቡን ተናግረዋል።

እንደ ኃላፊዋ ገለጻ በዘጠኝ ወራት የተሰበሰበው ገቢ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ከ7 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር በላይ ብልጫ አለው፡፡

ስኬታማ የግብር አሰባሰብ ሥራ ለማከናወንም ዘመናዊ የታክስ አሰባሰብ ስርዓትን ከመዘርጋት ባለፈ በግብር ሕጉ ላይ ግንዛቤ የማስጨበጥና የታክስ ህግን የማስከበር ሥራ መሰራቱን አስረድተዋል።

ከዚህ በተጨማሪ ሁሉንም የገቢ አማራጮች በአግባቡ ለመጠቀም ትኩረት ተሰጥቶ በመሰራቱ አበረታች ውጤት መመዝገቡን ገልጸዋል።

በቀሪ ወራትም በበጀት ዓመቱ ለመሰብሰብ የተያዘውን ዕቅድ ለማሳካት ክልሉ ያለውን የገቢ አማራጭ በአግባቡ ለመጠቀም በትኩረት ይሰራል ብለዋል፡፡

በሆሳዕና ከተማ የአጋፔ ሆቴልና ሪስቶራንት ባለቤት አቶ መላኩ መኮንን በበኩላቸው ግብርን በወቅቱና በታማኝነት መክፈል ለአካባቢ ልማት መፋጠን ያለው አስተዋጽኦ ከፍተኛ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡

የሚጠበቅባቸውን ግብር በወቅቱ በመክፈል የዜግነት ግዴታቸውን መወጣታቸውን ገልጸው፣ በተሰማሩበት የንግድ ሥራ ግብራቸውን በመክፈል ለአካባቢው ልማት የሚያደርጉትን አስተዋጽኦ እንደሚያጠናክሩም ተናግረዋል።

ሁሉም ዜጋ የሚጠበቅበትን ግብር በወቅቱ በመክፈል ለሀገር እድገትና ለዜጎች ተጠቃሚነት የበኩሉን አስተዋጽኦ ማድረግ ይጠበቅበታል ሲሉም ነው የገለጹት።


ግብርን በወቅቱ መክፈል ልማት በማፋጠን የህዝብን የልማት ፍላጎት ለማሟላት ያለው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ በሆሳዕና ከተማ የአቢሲኒያ የወንዶች ልብስ ስፌት ድርጅት ባለቤት አቶ ብርሃኑ አያሌው ናቸው፡፡

የደረጃ "ሐ" ግብር ከፋይ እንደሆኑ የገለጹት አቶ ብርሃኑ በየዓመቱ የሚጠበቅባቸውን ግብር በወቅቱ እንደሚከፍሉ ተናግረዋል፡፡

ግብር ለራስ ልማት እንደሚውል በመገንዘብ ያለማንም ቀስቃሽ ግብርን በወቅቱ የመክፈል ግዴታን መወጣት ያስፈልጋል ሲሉም ተናግረዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሚያዝያ እና ግንቦት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት ከምስል ጋር!

  የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...

Jun 4, 2026

በዲጂታል ክህሎት ራሳችንን እያበቃን ነው - ተማሪዎች

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...

Jun 1, 2026

በኦሮሚያ ክልል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ የአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት ተሰጥቷል

አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...

May 25, 2026

በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው

ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...

May 15, 2026