የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ገቢን አሟጦ ለመሰብሰብ በተደረገ ጥረት አበረታች ውጤት ተመዝግቧል 

Apr 17, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሆሳዕና፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ባለፉት ዘጠኝ ወራት ገቢን አሟጦ ለመሰብሰብ በተደረገ ጥረት አበረታች ውጤት መመዝገቡን የክልሉ ገቢዎች ቢሮ አስታወቀ፡፡

በክልሉ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ18 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ መቻሉም ተመላክቷል።

የቢሮው ኃላፊ ቀመሪያ ረሻድ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በክልሉ በህዝብ ለሚነሱ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ፈጣን ምላሽ ለመስጠት ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ በአግባቡ መሰብሰብ ያስፈልጋል።

በክልሉ በተያዘው በጀት ዓመት ከመደበኛና ከማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ከ27 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደ ተግባር መገባቱን አመልክተዋል።

በዚህም ባለፉት ዘጠኝ ወራት ገቢን አሟጦ ለመሰብሰብ በተደረገ ጥረት ከ18 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ በመሰብሰብ አበረታች ውጤት መመዝገቡን ተናግረዋል።

እንደ ኃላፊዋ ገለጻ በዘጠኝ ወራት የተሰበሰበው ገቢ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ከ7 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር በላይ ብልጫ አለው፡፡

ስኬታማ የግብር አሰባሰብ ሥራ ለማከናወንም ዘመናዊ የታክስ አሰባሰብ ስርዓትን ከመዘርጋት ባለፈ በግብር ሕጉ ላይ ግንዛቤ የማስጨበጥና የታክስ ህግን የማስከበር ሥራ መሰራቱን አስረድተዋል።

ከዚህ በተጨማሪ ሁሉንም የገቢ አማራጮች በአግባቡ ለመጠቀም ትኩረት ተሰጥቶ በመሰራቱ አበረታች ውጤት መመዝገቡን ገልጸዋል።

በቀሪ ወራትም በበጀት ዓመቱ ለመሰብሰብ የተያዘውን ዕቅድ ለማሳካት ክልሉ ያለውን የገቢ አማራጭ በአግባቡ ለመጠቀም በትኩረት ይሰራል ብለዋል፡፡

በሆሳዕና ከተማ የአጋፔ ሆቴልና ሪስቶራንት ባለቤት አቶ መላኩ መኮንን በበኩላቸው ግብርን በወቅቱና በታማኝነት መክፈል ለአካባቢ ልማት መፋጠን ያለው አስተዋጽኦ ከፍተኛ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡

የሚጠበቅባቸውን ግብር በወቅቱ በመክፈል የዜግነት ግዴታቸውን መወጣታቸውን ገልጸው፣ በተሰማሩበት የንግድ ሥራ ግብራቸውን በመክፈል ለአካባቢው ልማት የሚያደርጉትን አስተዋጽኦ እንደሚያጠናክሩም ተናግረዋል።

ሁሉም ዜጋ የሚጠበቅበትን ግብር በወቅቱ በመክፈል ለሀገር እድገትና ለዜጎች ተጠቃሚነት የበኩሉን አስተዋጽኦ ማድረግ ይጠበቅበታል ሲሉም ነው የገለጹት።


ግብርን በወቅቱ መክፈል ልማት በማፋጠን የህዝብን የልማት ፍላጎት ለማሟላት ያለው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ በሆሳዕና ከተማ የአቢሲኒያ የወንዶች ልብስ ስፌት ድርጅት ባለቤት አቶ ብርሃኑ አያሌው ናቸው፡፡

የደረጃ "ሐ" ግብር ከፋይ እንደሆኑ የገለጹት አቶ ብርሃኑ በየዓመቱ የሚጠበቅባቸውን ግብር በወቅቱ እንደሚከፍሉ ተናግረዋል፡፡

ግብር ለራስ ልማት እንደሚውል በመገንዘብ ያለማንም ቀስቃሽ ግብርን በወቅቱ የመክፈል ግዴታን መወጣት ያስፈልጋል ሲሉም ተናግረዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026