የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በምስራቅ ወለጋ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 95 ሺህ ወጣቶች በተለያዩ የስራ መስኮች ተሰማርተዋል

Apr 20, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ነቀምቴ ፤ሚያዚያ 10/2018 (ኢዜአ)፡-በምስራቅ ወለጋ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 95 ሺህ ወጣቶች ተደራጅተው በተለያዩ የስራ መስኮች መሰማራታቸውን የዞኑ የስራ እድል ፈጠራ እና ክህሎት ጽህፈት ቤት አስታወቀ።

የጽሕፈት ቤቱ ምክትል ኃላፊ ወይዘሮ ባጩ ተስፋዬ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ጽሕፈት ቤቱ የሥራ አጥነትን ችግር በማቃለል የአምራች ኃይሉን የልማት ተሳታፊነትና ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየሠራ ይገኛል።

በበጀት ዓመቱም ከ100 ሺህ የሚበልጡ ወጣቶችን በማደራጀት ወደ ሥራ ለማስገባት የታቀደ ሲሆን፣ እስካሁን ባለው ሒደት 95 ሺህ ወጣቶችን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን አስረድተዋል።

ወጣቶቹ ከተሰማሩባቸው መስኮች መካከል ግብርና እና ማኑፋክቸሪንግን ጨምሮ ሌሎች የገቢ ማስገኛ ፕሮግራሞችን በአብነት ጠቅሰዋል።

ወጣቶቹ በተሰማሩባቸው መስኮች ውጤታማ መሆን እንዲችሉም መንግሥት ከ700 ሚሊዮን ብር በላይ ብድር እንዳመቻቸላቸው ተናግረዋል።

ይህም የዞኑን ወጣቶች የሥራ ባሕል በመቀየር የልማት ተሳታፊና ተጠቃሚ እንዲሆኑ ምቹ መደላድል መፍጠሩን ገልጸዋል።

በዞኑ የሲቡ ስሬ ወረዳ የንግድ፣ የሥራ ዕድል ፈጠራ እና ኢንቨስትመንት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኢብሳ ዲለንሳ በበኩላቸው፤ ወጣቶች ከጠባቂነት ተላቀው ባላቸው ዕውቀት እና ጉልበት ሠርተው እንዲለወጡ በቅንጅት እየተሠራ መሆኑን ጠቁመዋል።

በዚህ ረገድ በበጀት ዓመቱ ከ9 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ወጣቶች የሥራ ዕድል ለማመቻቸት ታቅዶ ሲሠራ መቆየቱን ጠቅሰዋል።

ወጣቶቹን በ340 ኢንተርፕራይዞች በማደራጀት በአትክልትና ፍራፍሬ፣ በእንስሳት ማደለብና እርባታ፣ እንዲሁም በሌሎች መስኮች በመሰማራት የተሻለ ውጤት በማምጣት ላይ እንደሚገኙ አስረድተዋል።

የወረዳው አስተዳደርም ከ37 ሚሊዮን ብር በላይ ብድር በማቅረብ ኢንተርፕራይዞቹ እንዲጠናከሩ ድጋፍ ማድረጉን አብራርተዋል።

ከሥራ ዕድሉ ተጠቃሚዎች መካከል በብረታ ብረትና እንጨት ሥራ የተሰማራው ጪምዴሳ በዳሳ እንደሚለው፤ በዚህ ዓመት መንግሥት ባመቻቸላቸው ዕድል የ200 ሺህ ብር ብድር በመውሰድ ሥራ ጀምረዋል።

በተመቻቸላቸው ዕድል ጠንክረው በመሥራትም ከራሳቸው አልፎ ለሌሎች የሥራ ዕድል መፍጠር መቻላቸውን ይናገራል።

በአሁኑ ወቅትም ካፒታላቸውን ወደ 1 ሚሊዮን ብር በማሳደግ ተጠቃሚ መሆናቸውን አመልክቷል።

በወረዳው የሚገኙት የጫልቱ፣ ዓለምነሽ እና ጓደኞቻቸው ማህበር አባል ወጣት ምቲኬ አበራ፤ በተያዘው ዓመት በእንጀራ ንግድ ላይ ሥራ የጀመረው ማኅበራቸው ጥሩ ገቢ ማግኘት መጀመሩን ተናግራለች።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚው ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለአፍሪካ አገራት ትልቅ አርአያ ናቸው - የላይቤሪያ ልዑካን ቡድን

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...

Apr 16, 2026

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026

<p>ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በቦንጋ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው</p>

ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...

Feb 24, 2025

<p>በክልሉ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ እየተካሄደ ነው</p>

ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...

Feb 24, 2025