🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 12/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ልማት ባንክ ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን ስትራቴጂካዊ አጋርነት በማጠናከር፣ ለሀገሪቱ የልማት የቅድሚያ ትኩረቶች አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አስታወቀ።
የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት እና የዓለም ባንክ ዓመታዊ የፀደይ ወቅት ስብስባ በዋሺንግተን ዲሲ ተደርጓል።
የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ፣ ከስብሰባው ጎን ለጎን ከአፍሪካ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት ሲዲ ኡልድ ታህ (ዶ/ር) ጋር ውይይት አድርገዋል።
ውይይቱ ሁለንተናዊ ለውጥ የሚያመጡ የልማት ትብብሮችን ማሳደግን ያለመ ነው።

በኢትዮጵያና በአፍሪካ ልማት ባንክ መካከል ያለውን ጠንካራ አጋርነት መረጋገጥ የሚያሳይ መሆኑ ተገልጿል።
ባንኩ የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ሪፎርም ስራዎችና የረጅም ጊዜ የልማት ግቦችን ለማሳካት የሚጫወተው ወሳኝ ሚናም ተነስቷል።
ሚኒስትር አህመድ ሽዴ ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ የኢኮኖሚ ተግዳሮቶች ቢኖሩም የሪፎርም አጀንዳዋን ተግባራዊ በማድረግ ቀጣይነት ያለው እድገት እያስመዘገበች መሆኑን አመልክተዋል።
መንግስት ለማክሮ ኢኮኖሚ መረጋጋት፣ ለግሉ ዘርፍ መሪነት እና ለተቋማዊ ሽግግር በቁርጠኝነት እየሰራ ነው ብለዋል።
የአፍሪካ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት ሲዲ ኡልድ ታህ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ በሪፎርሙ እያመጣች ያለውን ለውጥና ተለዋዋጭ ሁኔታዎችን የመቋቋም አቅም አድንቀዋል።

ባንኩ ኢትዮጵያ ቅድሚያ ለምትሰጣቸው የልማት ጉዳዮች የሚያደርገውን ጠንካራ ድጋፍ እንደሚቀጥል አመልክተዋል።
ሁለቱ ወገኖች ሁሉን አቀፍ እድገትን ለማስቀጠልና የስራ እድል ፈጠራን ለማፋጠን ቁልፍ በሆኑት የኢነርጂ፣ የመሰረተ ልማት፣ የግብርና እና የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ዘርፎች ላይ ትብብራቸውን ይበልጥ ለማሳደግ ተስማምተዋል።
ኢትዮጵያና የአፍሪካ ልማት ባንክ ዘላቂ የኢኮኖሚ ሽግግርን ለማምጣትና ስትራቴጂካዊ አጋርነታቸውን ለማላቅ ያላቸውን ቁርጠኝነት መግለጻቸውን የገንዘብ ሚኒስቴር ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል።
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025