የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የአፍሪካ ልማት ባንክ ለኢትዮጵያ የልማት አጀንዳዎች ያለውን አጋርነት እንደሚቀጥል ገለጸ

Apr 21, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 12/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ልማት ባንክ ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን ስትራቴጂካዊ አጋርነት በማጠናከር፣ ለሀገሪቱ የልማት የቅድሚያ ትኩረቶች አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አስታወቀ።

የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት እና የዓለም ባንክ ዓመታዊ የፀደይ ወቅት ስብስባ በዋሺንግተን ዲሲ ተደርጓል።

የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ፣ ከስብሰባው ጎን ለጎን ከአፍሪካ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት ሲዲ ኡልድ ታህ (ዶ/ር) ጋር ውይይት አድርገዋል።

ውይይቱ ሁለንተናዊ ለውጥ የሚያመጡ የልማት ትብብሮችን ማሳደግን ያለመ ነው።


በኢትዮጵያና በአፍሪካ ልማት ባንክ መካከል ያለውን ጠንካራ አጋርነት መረጋገጥ የሚያሳይ መሆኑ ተገልጿል።

ባንኩ የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ሪፎርም ስራዎችና የረጅም ጊዜ የልማት ግቦችን ለማሳካት የሚጫወተው ወሳኝ ሚናም ተነስቷል።

ሚኒስትር አህመድ ሽዴ ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ የኢኮኖሚ ተግዳሮቶች ቢኖሩም የሪፎርም አጀንዳዋን ተግባራዊ በማድረግ ቀጣይነት ያለው እድገት እያስመዘገበች መሆኑን አመልክተዋል።

መንግስት ለማክሮ ኢኮኖሚ መረጋጋት፣ ለግሉ ዘርፍ መሪነት እና ለተቋማዊ ሽግግር በቁርጠኝነት እየሰራ ነው ብለዋል።

የአፍሪካ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት ሲዲ ኡልድ ታህ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ በሪፎርሙ እያመጣች ያለውን ለውጥና ተለዋዋጭ ሁኔታዎችን የመቋቋም አቅም አድንቀዋል።


ባንኩ ኢትዮጵያ ቅድሚያ ለምትሰጣቸው የልማት ጉዳዮች የሚያደርገውን ጠንካራ ድጋፍ እንደሚቀጥል አመልክተዋል።

ሁለቱ ወገኖች ሁሉን አቀፍ እድገትን ለማስቀጠልና የስራ እድል ፈጠራን ለማፋጠን ቁልፍ በሆኑት የኢነርጂ፣ የመሰረተ ልማት፣ የግብርና እና የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ዘርፎች ላይ ትብብራቸውን ይበልጥ ለማሳደግ ተስማምተዋል።

ኢትዮጵያና የአፍሪካ ልማት ባንክ ዘላቂ የኢኮኖሚ ሽግግርን ለማምጣትና ስትራቴጂካዊ አጋርነታቸውን ለማላቅ ያላቸውን ቁርጠኝነት መግለጻቸውን የገንዘብ ሚኒስቴር ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሚያዝያ እና ግንቦት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት ከምስል ጋር!

  የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...

Jun 4, 2026

በዲጂታል ክህሎት ራሳችንን እያበቃን ነው - ተማሪዎች

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...

Jun 1, 2026

በኦሮሚያ ክልል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ የአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት ተሰጥቷል

አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...

May 25, 2026

በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው

ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...

May 15, 2026