የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሪፎርም ድጋፉን እንደሚያጠናክር ገለጸ

Apr 21, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 12/2018 (ኢዜአ)፦ የዓለም ባንክ በኢትዮጵያ ለሚከናወኑ የኢኮኖሚ ሪፎርም ስራዎች ያለውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋገጠ።

የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት እና የዓለም ባንክ የፀደይ ወቅት ስብሰባ በዋሺንግተን ዲሲ ተካሄዷል።

በገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ የተመራ ከፍተኛ ልዑክ ከስብሰባው ጎን ለጎን ከዓለም ባንክ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ፓስካል ዶኖሆ ጋር ውይይት አድርጓል።

ሚኒስትሩ በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ (Homegrown Economic Reform Agenda) የተመዘገቡ ውጤቶችን ያብራሩ ሲሆን፤ በተለይም በኢኮኖሚ መረጋጋትና በመዋቅራዊ ሽግግር ረገድ የተመዘገቡ ስኬቶችን አንስተዋል።

ኢትዮጵያ ወደ ግል ዘርፍ መር የኢኮኖሚ እድገት በምታደርገው ሽግግር፣ የግል ካፒታልን ማሰባሰብ አሁን ላይ ዋነኛው ትኩረት መሆኑን ሚኒስትሩ አፅንኦት የሰጡት ጉዳይ ነው።


በተጨማሪም ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ 32ኛውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት (COP32) ጉባኤን ለማስተናገድ እያደረገችው ስላለው ዝግጅት ለዳይሬክተሩ ገለጻ አድርገዋል።

ጉባኤው የኢትዮጵያን የአየር ንብረት መቋቋም አቅምና የአረንጓዴ ልማት ቃል ኪዳኖችን እውን ለማድረግ ያለውን ጉልህ ፋይዳ ጠቁመዋል።

የዓለሞ ባንክ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ፓስካል ዶኖሆ በበኩላቸው የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።

የኢኮኖሚ ማሻሻያ እርምጃዎቹ ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የሚያደርጋቸውን ድጋፎች ለማሳደግ ቁርጠኛ መሆኑንም አመልክተዋል።

ዳይሬክተሩ ለኢትዮጵያ የኮፕ 32 ጉባኤ ዝግጅትም ድጋፍ ለማድረግ ቃል የገቡ ሲሆን፣ በኢትዮጵያ የሥራ ጉብኝት ለማድረግ ዝግጁ እንደሆኑ መግለጻቸውን የገንዘብ ሚኒስቴር ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል።

Boost this post to get more reach forEthiopian News

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚው ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለአፍሪካ አገራት ትልቅ አርአያ ናቸው - የላይቤሪያ ልዑካን ቡድን

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...

Apr 16, 2026

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026

<p>ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በቦንጋ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው</p>

ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...

Feb 24, 2025

<p>በክልሉ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ እየተካሄደ ነው</p>

ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...

Feb 24, 2025