🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 12/2018 (ኢዜአ)፦ የዓለም ባንክ በኢትዮጵያ ለሚከናወኑ የኢኮኖሚ ሪፎርም ስራዎች ያለውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋገጠ።
የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት እና የዓለም ባንክ የፀደይ ወቅት ስብሰባ በዋሺንግተን ዲሲ ተካሄዷል።
በገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ የተመራ ከፍተኛ ልዑክ ከስብሰባው ጎን ለጎን ከዓለም ባንክ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ፓስካል ዶኖሆ ጋር ውይይት አድርጓል።
ሚኒስትሩ በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ (Homegrown Economic Reform Agenda) የተመዘገቡ ውጤቶችን ያብራሩ ሲሆን፤ በተለይም በኢኮኖሚ መረጋጋትና በመዋቅራዊ ሽግግር ረገድ የተመዘገቡ ስኬቶችን አንስተዋል።
ኢትዮጵያ ወደ ግል ዘርፍ መር የኢኮኖሚ እድገት በምታደርገው ሽግግር፣ የግል ካፒታልን ማሰባሰብ አሁን ላይ ዋነኛው ትኩረት መሆኑን ሚኒስትሩ አፅንኦት የሰጡት ጉዳይ ነው።

በተጨማሪም ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ 32ኛውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት (COP32) ጉባኤን ለማስተናገድ እያደረገችው ስላለው ዝግጅት ለዳይሬክተሩ ገለጻ አድርገዋል።
ጉባኤው የኢትዮጵያን የአየር ንብረት መቋቋም አቅምና የአረንጓዴ ልማት ቃል ኪዳኖችን እውን ለማድረግ ያለውን ጉልህ ፋይዳ ጠቁመዋል።
የዓለሞ ባንክ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ፓስካል ዶኖሆ በበኩላቸው የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
የኢኮኖሚ ማሻሻያ እርምጃዎቹ ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የሚያደርጋቸውን ድጋፎች ለማሳደግ ቁርጠኛ መሆኑንም አመልክተዋል።
ዳይሬክተሩ ለኢትዮጵያ የኮፕ 32 ጉባኤ ዝግጅትም ድጋፍ ለማድረግ ቃል የገቡ ሲሆን፣ በኢትዮጵያ የሥራ ጉብኝት ለማድረግ ዝግጁ እንደሆኑ መግለጻቸውን የገንዘብ ሚኒስቴር ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል።
Boost this post to get more reach forEthiopian News
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026