የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ በአማራ ክልል የቱሪዝም ኢንዱስትሪውን ያነቃቁ ውጤታማ ሥራዎች ተከናውነዋል

Apr 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ባህር ዳር፤ ሚያዝያ 14/2018(ኢዜአ)- ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ በአማራ ክልል የቱሪዝም ኢንዱስትሪውን ያነቃቁ ውጤታማ ሥራዎች መከናወናቸውን የክልሉ ባህል፣ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ አስታወቀ።

ቢሮው ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከቱሪዝም ዘርፉ 12 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰቡን ገልጿል።

የቢሮው ሃላፊ አቶ መልካሙ ፀጋዬ ለኢዜአ እንደገለጹት ክልሉ ያለውን እምቅ የቱሪስት ሃብት በተለያዩ የመገናኛ ብዙሃን አማራጮች ከማስተዋወቅ ባለፈ አዳዲስ መዳረሻዎችን ወደ ሥራ ለማስገባት ሰፋፊ ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ።

በዚህም ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ የክልሉን የቱሪሰት እንቅስቃሴ ያነቃቁ ውጤታማ ሥራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል።

ባለፉት ዘጠኝ ወራትም ከቱሪዝም ዘርፉ 12 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰቡን አስረድተዋል።

በዚሁ ወቅት 16 ነጥብ 7 ሚሊዮን የሃገር ውስጥና የውጭ ሀገራት ቱሪስቶች በክልሉ የሚገኙ የመስህብ ሃብቶችን እንደጎበኙ ተናግረዋል።

የለውጡ መንግስት ትኩረት ከሰጣቸው አምስት የኢኮኖሚ ዘርፎች መካከል አንዱ ቱሪዝም መሆኑን ገልጸው ዘርፉን በተሻለ መጠቀም የሚያስችሉ በርካታ የልማት ሥራዎችም እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል።

ቱሪስቶቹ የፋሲል አብያተ መንግስታት፣ የሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ፣ የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያንን ጨምሮ ሌሎች መዳረሻ ቦታዎችን ጎብኝተዋል ብለዋል።

በተጨማሪም በሻደይ፣ አሸንድዬ፣ ሶለል፣ ገና፣ ጥምቀት፣ አገው ፈረሰኞች ማህበር በዓላት እንዲሁም በሃይማኖታዊና ባህላዊ ሁነቶች መታደማቸውንም ተናግረዋል።

የተገኘውን ውጤት አጠናክሮ ለማስቀጠልም 27 ቅርሶችን የመጠገን፣ ቅርሶችን የማሰባሰብ፣ ሙዚየሞችን የመገንባትና መሰረተ ልማቶችን የማስፋት ሥራ እየተከናወነ መሆኑንም ጠቁመዋል።

በገበታ ለሃገርና በገበታ ለትውልድ የተገነቡት የጎርጎራ ኢኮ ሪዞርት እና የሎጎ ሃይቅ ሪዞርት ተጨማሪ መዳረሻ ከመሆን ባሻገር ቱሪስቶች ደረጃውን የጠበቀ አገልግሎት እንዲያገኙና የቆይታ ጊዜያቸው እንዲራዘም ያገዙ መሆኑን ገልፀዋል።

የተገኘውን ስኬት አጠናክሮ ለማስቀጠልም የዘርፉ የ25 ዓመት አሻጋሪ የልማት ዕቅድና የአምስት ዓመት ስትራቴጅክ ዕቅድ ወጥቶ እየተተገበረ እንደሆነ አብራርተዋል።

በአሻጋሪ የልማት ዕቅዱ መሰረት ጣናን፣ ሰከላን፣ አንኮበርን፣ ጎንደርንና መሰል አካባቢዎችን መነሻ ያደረጉ 10 ወሳኝ አዳዲስ መዳረሻዎችን ለመገንባት መታቀዱንም አመልክተዋል።

Ethiopian News Agency #ኢዜአ #ቱሪዝም

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ ነው -ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚው ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለአፍሪካ አገራት ትልቅ አርአያ ናቸው - የላይቤሪያ ልዑካን ቡድን

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...

Apr 16, 2026

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026

<p>ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በቦንጋ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው</p>

ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...

Feb 24, 2025