🔇Unmute
ባህር ዳር፤ ሚያዝያ 14/2018(ኢዜአ)- ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ በአማራ ክልል የቱሪዝም ኢንዱስትሪውን ያነቃቁ ውጤታማ ሥራዎች መከናወናቸውን የክልሉ ባህል፣ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ አስታወቀ።
ቢሮው ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከቱሪዝም ዘርፉ 12 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰቡን ገልጿል።
የቢሮው ሃላፊ አቶ መልካሙ ፀጋዬ ለኢዜአ እንደገለጹት ክልሉ ያለውን እምቅ የቱሪስት ሃብት በተለያዩ የመገናኛ ብዙሃን አማራጮች ከማስተዋወቅ ባለፈ አዳዲስ መዳረሻዎችን ወደ ሥራ ለማስገባት ሰፋፊ ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ።
በዚህም ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ የክልሉን የቱሪሰት እንቅስቃሴ ያነቃቁ ውጤታማ ሥራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል።
ባለፉት ዘጠኝ ወራትም ከቱሪዝም ዘርፉ 12 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰቡን አስረድተዋል።
በዚሁ ወቅት 16 ነጥብ 7 ሚሊዮን የሃገር ውስጥና የውጭ ሀገራት ቱሪስቶች በክልሉ የሚገኙ የመስህብ ሃብቶችን እንደጎበኙ ተናግረዋል።
የለውጡ መንግስት ትኩረት ከሰጣቸው አምስት የኢኮኖሚ ዘርፎች መካከል አንዱ ቱሪዝም መሆኑን ገልጸው ዘርፉን በተሻለ መጠቀም የሚያስችሉ በርካታ የልማት ሥራዎችም እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል።
ቱሪስቶቹ የፋሲል አብያተ መንግስታት፣ የሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ፣ የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያንን ጨምሮ ሌሎች መዳረሻ ቦታዎችን ጎብኝተዋል ብለዋል።
በተጨማሪም በሻደይ፣ አሸንድዬ፣ ሶለል፣ ገና፣ ጥምቀት፣ አገው ፈረሰኞች ማህበር በዓላት እንዲሁም በሃይማኖታዊና ባህላዊ ሁነቶች መታደማቸውንም ተናግረዋል።
የተገኘውን ውጤት አጠናክሮ ለማስቀጠልም 27 ቅርሶችን የመጠገን፣ ቅርሶችን የማሰባሰብ፣ ሙዚየሞችን የመገንባትና መሰረተ ልማቶችን የማስፋት ሥራ እየተከናወነ መሆኑንም ጠቁመዋል።
በገበታ ለሃገርና በገበታ ለትውልድ የተገነቡት የጎርጎራ ኢኮ ሪዞርት እና የሎጎ ሃይቅ ሪዞርት ተጨማሪ መዳረሻ ከመሆን ባሻገር ቱሪስቶች ደረጃውን የጠበቀ አገልግሎት እንዲያገኙና የቆይታ ጊዜያቸው እንዲራዘም ያገዙ መሆኑን ገልፀዋል።
የተገኘውን ስኬት አጠናክሮ ለማስቀጠልም የዘርፉ የ25 ዓመት አሻጋሪ የልማት ዕቅድና የአምስት ዓመት ስትራቴጅክ ዕቅድ ወጥቶ እየተተገበረ እንደሆነ አብራርተዋል።
በአሻጋሪ የልማት ዕቅዱ መሰረት ጣናን፣ ሰከላን፣ አንኮበርን፣ ጎንደርንና መሰል አካባቢዎችን መነሻ ያደረጉ 10 ወሳኝ አዳዲስ መዳረሻዎችን ለመገንባት መታቀዱንም አመልክተዋል።
Ethiopian News Agency #ኢዜአ #ቱሪዝም
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025