🔇Unmute
ሰመራ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡- መንግስት ለህብረተሰቡ የመልካም አስተዳደር እና የልማት ጥያቄዎች ምላሽ በመስጠት በየደረጃው ያለውን የዜጎች ተጠቃሚነት ማሳደግ መቻሉን የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አወል አርባ ገለጹ።
የአይሳኢታ አፋምቦ የብዙሃን መንደር የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክትና የአይሳኢታ ከተማ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልግሎት በቅተዋል።

በመርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አወል አርባ፤ የተከናወነው የልማት ፕሮጀክት የህብረተሰቡን ጥያቄዎች በተግባር ከመመለሱም በላይ፣ በየደረጃው ያለውን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ያስቻለ መሆኑን ገልጸዋል።
ከምንም በላይ ለአፋር ህዝብ ውሃ አስፈላጊ መሆኑን ገልፀው፤ የተደመረ አቅምን በማላቅና በማስተባበር ለውጤት የበቃው ይህ ፕሮጀክት በዚህ ረገድ ጉልህ አበርክቶ አለው ብለዋል።

በዛሬው ዕለት የተመረቁት ፕሮጀክቶች በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴርና በዩኒሴፍ ድጋፍ ከ800 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው መሆኑንም አንስተው፤ ተቋማቱን አመስግነዋል።
በፕሮጀክቶቹ ተጠቃሚ የሆኑ ሁለቱ ወረዳዎች ለዘላቂነቱ ትኩረት በመስጠት በተገቢው ማስተዳደር እንደሚገባቸው አስገንዝበዋል።
የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር) እንደገለጹት፤ መንግስት እንደ አፋር ክልል ያሉ የውሃ ሽፋን አነስተኛ ለሆነባቸው አካባቢዎች ልዩ ትኩረት በመስጠት፣ በፕሮጀክቶች ታግዞ መስራት እንደሚገባ በጽኑ ያምናል ብለዋል።

ሚኒስትሩ አክለውም፣ በለውጡ መንግስት የተከናወኑ የተቀናጁ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ጠቁመው፤ በዚህም የአገራችን የንጹህ መጠጥ ውሃ ተደራሽነት ወደ 72.5 በመቶ ከፍ ማለቱን አረጋግጠዋል።
የአፋር ክልል ውሃና ኢነርጂ ቢሮ ኀላፊ አቶ አህመድ ሻሚ በበኩላቸው፤ የአይሳኢታ ከተማና የአይሳኢታ አፋምቦ የብዙሃን መንደር የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ያሳደገ ነው ብለዋል።

ፕሮጀክቱ የአይሳኢታና አፋምቦ ስምንት ቀበሌዎች ከ52 ሺህ በላይ ቤተሰቦችን ተጠቃሚ የሚያደርግ መሆኑን ገልፀዋል።
በምረቃ መርሃ ግብሩ ላይ የፌዴራልና የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኀላፊዎችና የአይሳኢታና አፋምቦ ወረዳ ነዋሪዎች ተገኝተዋል።
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025