የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በተተገበሩ የሪፎርም ስራዎች የግብርና ዘርፉን ወደ ሜካናይዜሽን ማሸጋገር ያስቻሉ ተጨባጭ ወጤቶች ተመዝግበዋል

Apr 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡- ባለፉት የለውጥ ዓመታት በኢትዮጵያ የተተገበሩ የሪፎርም ስራዎች የግብርና ዘርፉን ወደ ሜካናይዜሽን ማሸጋገር ያስቻሉ ተጨባጭ ውጤቶች መመዝገባቸውን የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ ገለጹ።

የ2018 በጀት ዓመት ሦስተኛው የመቶ ቀናት እና የዘጠኝ ወራት ስራ አፈጻጸም ሪፖርት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ተገምግሟል።

የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ በሰጡት ማብራሪያ፣ በኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት የተተገበሩ የሪፎርም ስራዎች የግብርና ዘርፉን ወደ ሜካናይዜሽን ማሸጋገር የሚያስችሉ ተጨባጭ ለውጦች መመዝገባቸውን ገልፀዋል።

በዚህም አጠቃላይ ኢኮኖሚው ወደ ፊት እንዲራመድ፣ ፈጣንንና ጥራት ያለው ኢኮኖሚ እንዲመዘገብ በማስቻል ሁሉንም ተጠቃሚ የሚያደርግ እድገት መመዝገቡን ጠቁመዋል።

ከዚህ ቀደም ዝቅተኛ የግብርና ማሽነሪ ቁጥር ለማሳደግ መንግሥት የፖሊሲ ማበረታቻ በማድረግ አርሶ አደሮቹ ማሽነሪዎችን ከቀረጥ ነፃ እንዲያስገቡ እና የብድር አቅርቦት በማመቻቸት ሰፊ ስራ መሰራቱን አንስተዋል።

በዚህም ባለፉት የለውጥ ዓመታት በተሰራው ስራ ወደ 27 ሺህ ትራክተሮች ከ8 ሺህ በላይ ኮምባይነሮች እንዲሁም ከ280 ሺህ በላይ በሞተር የሚሰሩ ፓምፖች ተደራሽ ማድርግ መቻሉን ተናግረዋል።

በዚህም የግብርናው ስራ ከዝማላዳዊ አሰራር ተላቆ ወደ ሜካናይዜሽን እየተሸጋገረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ባለፉት አመታት በተሰራ ስራ የሜካናይዜሽን እድገቱ 72 በመቶ መድረሱን ያሳያል ነው ያሉት።

አጠቃላይ በኢትዮጵያ በትራክተር የሚለማ መሬት 7 ሚሊየን ሄክታር መሬት የደረሰ ሲሆን ይህ ማለት ከሚለማው መሬት አንድ ሶስተኛውን በትራክተር ማልማት እንደተቻለ ገልፀዋል።

ይህም ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ለገበያ የሚቀርበውን ምርት በማሳደግ የአርሶ አደሩን ህይወት በመቀየር ረገድ ትልቅ ለውጥ ማስመዝገቡን ጠቁመዋል።

በመሆኑም ባለፉት የለውጥ አመታት ተግባራዊ የተደረገው ሪፎርም የግብርና ትራንስፎርሜሽንን ለማረጋገጥ ትልቅ አቅም የፈጠረ መሆኑን ተናግረዋል።

በዚህም ግብርናውን ከዝናብ ጥገኝነት ወደ መስኖ ለማሸጋገር በተደረገው ጥረት የመስኖ ልማት ሽፋኑ ከዓመት ወደ ዓመት እየጨመረ መጥቷል ነው ያሉት።

በዘንድሮው ዓመት ብቻ 4 ነጥብ 2 ሚሊየን ሄክታር መሬት በመስኖ ስንዴ ለማልማት ታቅዶ እስካሁን ወደ 3 ነጥብ 87 ሚሊየን ሄክታር ማልማት መቻሉን ጠቅሰዋል።

ይህም አርሶ አደሩ ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ በዓመት ሁለትና ከዚያ በላይ እንዲያመርት በማድረግ እንደ ሀገር የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የተያዘውን ግብ ለማሳካት ተጨባጭ ለውጥ ማሳየቱን ተናግረዋል። በተጨማሪም ለዜጎች ሰፋፊ የስራ እድል እየፈጠረ እንደሚገኝም ገልጸዋል።

አርሶ አደሩ ከምግብነት ባለፈ በመጠንም በጥራትም ተወዳዳሪ ምርቶችን በማምረት ለዓለም ገበያ ተደራሽ እያደረጉ መሆኑን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ ነው -ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚው ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለአፍሪካ አገራት ትልቅ አርአያ ናቸው - የላይቤሪያ ልዑካን ቡድን

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...

Apr 16, 2026

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026

<p>ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በቦንጋ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው</p>

ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...

Feb 24, 2025