የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በተተገበሩ የሪፎርም ስራዎች የግብርና ዘርፉን ወደ ሜካናይዜሽን ማሸጋገር ያስቻሉ ተጨባጭ ወጤቶች ተመዝግበዋል

Apr 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡- ባለፉት የለውጥ ዓመታት በኢትዮጵያ የተተገበሩ የሪፎርም ስራዎች የግብርና ዘርፉን ወደ ሜካናይዜሽን ማሸጋገር ያስቻሉ ተጨባጭ ውጤቶች መመዝገባቸውን የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ ገለጹ።

የ2018 በጀት ዓመት ሦስተኛው የመቶ ቀናት እና የዘጠኝ ወራት ስራ አፈጻጸም ሪፖርት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ተገምግሟል።

የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ በሰጡት ማብራሪያ፣ በኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት የተተገበሩ የሪፎርም ስራዎች የግብርና ዘርፉን ወደ ሜካናይዜሽን ማሸጋገር የሚያስችሉ ተጨባጭ ለውጦች መመዝገባቸውን ገልፀዋል።

በዚህም አጠቃላይ ኢኮኖሚው ወደ ፊት እንዲራመድ፣ ፈጣንንና ጥራት ያለው ኢኮኖሚ እንዲመዘገብ በማስቻል ሁሉንም ተጠቃሚ የሚያደርግ እድገት መመዝገቡን ጠቁመዋል።

ከዚህ ቀደም ዝቅተኛ የግብርና ማሽነሪ ቁጥር ለማሳደግ መንግሥት የፖሊሲ ማበረታቻ በማድረግ አርሶ አደሮቹ ማሽነሪዎችን ከቀረጥ ነፃ እንዲያስገቡ እና የብድር አቅርቦት በማመቻቸት ሰፊ ስራ መሰራቱን አንስተዋል።

በዚህም ባለፉት የለውጥ ዓመታት በተሰራው ስራ ወደ 27 ሺህ ትራክተሮች ከ8 ሺህ በላይ ኮምባይነሮች እንዲሁም ከ280 ሺህ በላይ በሞተር የሚሰሩ ፓምፖች ተደራሽ ማድርግ መቻሉን ተናግረዋል።

በዚህም የግብርናው ስራ ከዝማላዳዊ አሰራር ተላቆ ወደ ሜካናይዜሽን እየተሸጋገረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ባለፉት አመታት በተሰራ ስራ የሜካናይዜሽን እድገቱ 72 በመቶ መድረሱን ያሳያል ነው ያሉት።

አጠቃላይ በኢትዮጵያ በትራክተር የሚለማ መሬት 7 ሚሊየን ሄክታር መሬት የደረሰ ሲሆን ይህ ማለት ከሚለማው መሬት አንድ ሶስተኛውን በትራክተር ማልማት እንደተቻለ ገልፀዋል።

ይህም ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ለገበያ የሚቀርበውን ምርት በማሳደግ የአርሶ አደሩን ህይወት በመቀየር ረገድ ትልቅ ለውጥ ማስመዝገቡን ጠቁመዋል።

በመሆኑም ባለፉት የለውጥ አመታት ተግባራዊ የተደረገው ሪፎርም የግብርና ትራንስፎርሜሽንን ለማረጋገጥ ትልቅ አቅም የፈጠረ መሆኑን ተናግረዋል።

በዚህም ግብርናውን ከዝናብ ጥገኝነት ወደ መስኖ ለማሸጋገር በተደረገው ጥረት የመስኖ ልማት ሽፋኑ ከዓመት ወደ ዓመት እየጨመረ መጥቷል ነው ያሉት።

በዘንድሮው ዓመት ብቻ 4 ነጥብ 2 ሚሊየን ሄክታር መሬት በመስኖ ስንዴ ለማልማት ታቅዶ እስካሁን ወደ 3 ነጥብ 87 ሚሊየን ሄክታር ማልማት መቻሉን ጠቅሰዋል።

ይህም አርሶ አደሩ ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ በዓመት ሁለትና ከዚያ በላይ እንዲያመርት በማድረግ እንደ ሀገር የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የተያዘውን ግብ ለማሳካት ተጨባጭ ለውጥ ማሳየቱን ተናግረዋል። በተጨማሪም ለዜጎች ሰፋፊ የስራ እድል እየፈጠረ እንደሚገኝም ገልጸዋል።

አርሶ አደሩ ከምግብነት ባለፈ በመጠንም በጥራትም ተወዳዳሪ ምርቶችን በማምረት ለዓለም ገበያ ተደራሽ እያደረጉ መሆኑን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026