🔇Unmute
ባሕርዳር፤ ሚያዝያ 15/2018 (ኢዜአ)፡- ተቋማቸው ባካሄደው የሪፎርም ትግበራ በቴክኖሎጂ የታገዘ ቀልጣፋ የፍትሕ አገልግሎት መስጠት መቻሉን የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ዓለምአንተ አግደው ገለጹ።
የጠቅላይ ፍርድ ቤቱ የዘጠኝ ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ ተካሂዷል።

በዚሁ ወቅትም አቶ ዓለምአንተ እንደገለጹት፤ የፍርድ ቤቶችን አገልግሎት ዲጂታላይዝ ለማድረግ የተቀረጸው የሦስት ዓመት ስትራቴጂ አተገባበር ተስፋ ሰጭ ውጤቶችን እያሳየ መሆኑን ተናግረዋል።
በመጀመሪያው ምዕራፍ የታቀዱ የመሠረተ-ልማት ዝርጋታ፣ የኔትወርክ ሥራዎች እና የስማርት ችሎቶች ግንባታ ሥራዎች በስኬት መከናወናቸውን አንስተዋል።
ይህም ባለጉዳዮች ባሉበት ሆነው በኢ-ፋይሊንግ ሥርዓት ክስ መመስረት፣ ይግባኝ መጠየቅና የጉዳያቸውን ሂደት በሞባይል መተግበሪያ መከታተል የሚያስችል ዘመናዊ አሠራር ሥራ ላይ መዋሉን አስረድተዋል።
በቪዲዮ ኮንፈረንስ የሚታገዙ ስማርት ችሎቶች በመዘርጋታቸውም ሕብረተሰቡ ካለበት ሆኖ ክርክሩን እንዲያካሂድ በማድረግ የባለጉዳዮችን ወጪና እንግልት መቀነስ ተችሏል ነው ያሉት።

የጠቅላይ ፍርድ ቤቱ የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ዳይሬክተር መኳንንት አገኘሁ (ዶ/ር)፤ የፍርድ ቤቶችን አሠራር ዘመናዊ በማድረግ ቀልጣፋና ፍትሐዊ አገልግሎት ለመስጠት፣ የፍትሕ ተደራሽነትን ለማስፋት፣ የዳኝነት አገልግሎት ጥራትን በማሻሻል የሕዝብን እርካታ ለማረጋገጥ ያስቻሉ ተግባራት ተከናውነዋል ብለዋል።
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025