የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በዞኑ በበጋ መስኖ ተመርተው ለገበያ የቀረቡ ምርቶች ገበያን ማረጋጋት ችለዋል

Apr 29, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጎንደር፤ ሚያዝያ 20/2018 (ኢዜአ)፡- በማዕከላዊ ጎንደር ዞን በበጋ የመስኖ ልማት ተመርቶ ለገበያ የቀረበ ከ4 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት ገበያውን በማረጋጋት አስተዋጽኦ ማበርከቱን የዞኑ ግብርና መምሪያ ገለጸ።

በመምሪያው የመስኖ ልማት ቡድን መሪ ሀውልቱ ታደሰ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ በዞኑ በበጋው ወራቶች ሁሉንም የውሃ አማራጮች በመጠቀም ከ48 ሺህ ሔክታር በላይ በመስኖ ማልማት ተችሏል፡፡


ይህም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በ15 ሺህ ሔክታር፤ የተገኘው ምርትም በ1 ሚሊየን ኩንታል ብልጫ እንዳለው ተናግረዋል።

አርሶ አደሩ ገበያን መሰረት አድርጎ እንዲሠራ በተደረገለት ድጋፍና ክትትል መሰረትም፤ ጤፍ፣ ሩዝ፣ በቆሎ፣ ቲማቲም፣ ሽንኩርት፣ ድንችና ጥቅል ጎመን በማምረት ለገበያ ማቅረብ መቻሉን ገልጸዋል።

በአይነትም ሆነ በብዛት ተመርቶ ለገበያ የቀረበው ምርት የገበያ ዋጋን ከማረጋጋቱ ባለፈ፤ ሸማቹ ማህበረሰብ በተመጣጣኝ ዋጋ ምርቶቹን እንዲያገኝ አስቻይ ሁኔታ መፍጠር ተችሏል ብለዋል።

አርሶ አደሩ ምርታማነትን የሚያሳድጉ የግብርና ቴክኖሎጂዎችንና አሰራሮችን በስፋት በመጠቀም ለዘመናዊ የመስኖ ልማት መስፋፋት ትኩረት መስጠቱንም ገልጸዋል፡፡

በዚሁ ወቅት ለመስኖ አልሚ አርሶ አደሮች ከ4 ሺህ በላይ የውሃ መሳቢያ ሞተሮችን ጨምሮ ከ50 ሺህ ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያና ምርጥ ዘር በማቅረብ ለመስኖ ልማቱ ድጋፍ መደረጉን አስረድተዋል፡፡

በዞኑ የተገነቡ አነስተኛ፣ መካከለኛና ከፍተኛ የመስኖ አውታሮችም አርሶ አደሩ ከዝናብ ጥገኝነት ተላቆ በዓመት እስከ ሶስት ጊዜ ማምረት የሚችልበትን እድል ፈጥረዋል ነው ያሉት።


አንደኛው ዙር የመስኖ ልማት ተጠናቆ ሁለተኛው ዙር መጀመሩን ጠቁመው በአሁኑ ወቅትም፤ ከ10 ሺህ ሔክታር በላይ መሬት በመስኖ እየለማ እንደሚገኝ አመልክተዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሚያዝያ እና ግንቦት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት ከምስል ጋር!

  የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...

Jun 4, 2026

በዲጂታል ክህሎት ራሳችንን እያበቃን ነው - ተማሪዎች

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...

Jun 1, 2026

በኦሮሚያ ክልል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ የአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት ተሰጥቷል

አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...

May 25, 2026

በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው

ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...

May 15, 2026