🔇Unmute
ጎንደር፤ ሚያዝያ 20/2018 (ኢዜአ)፡- በማዕከላዊ ጎንደር ዞን በበጋ የመስኖ ልማት ተመርቶ ለገበያ የቀረበ ከ4 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት ገበያውን በማረጋጋት አስተዋጽኦ ማበርከቱን የዞኑ ግብርና መምሪያ ገለጸ።
በመምሪያው የመስኖ ልማት ቡድን መሪ ሀውልቱ ታደሰ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ በዞኑ በበጋው ወራቶች ሁሉንም የውሃ አማራጮች በመጠቀም ከ48 ሺህ ሔክታር በላይ በመስኖ ማልማት ተችሏል፡፡

ይህም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በ15 ሺህ ሔክታር፤ የተገኘው ምርትም በ1 ሚሊየን ኩንታል ብልጫ እንዳለው ተናግረዋል።
አርሶ አደሩ ገበያን መሰረት አድርጎ እንዲሠራ በተደረገለት ድጋፍና ክትትል መሰረትም፤ ጤፍ፣ ሩዝ፣ በቆሎ፣ ቲማቲም፣ ሽንኩርት፣ ድንችና ጥቅል ጎመን በማምረት ለገበያ ማቅረብ መቻሉን ገልጸዋል።
በአይነትም ሆነ በብዛት ተመርቶ ለገበያ የቀረበው ምርት የገበያ ዋጋን ከማረጋጋቱ ባለፈ፤ ሸማቹ ማህበረሰብ በተመጣጣኝ ዋጋ ምርቶቹን እንዲያገኝ አስቻይ ሁኔታ መፍጠር ተችሏል ብለዋል።
አርሶ አደሩ ምርታማነትን የሚያሳድጉ የግብርና ቴክኖሎጂዎችንና አሰራሮችን በስፋት በመጠቀም ለዘመናዊ የመስኖ ልማት መስፋፋት ትኩረት መስጠቱንም ገልጸዋል፡፡
በዚሁ ወቅት ለመስኖ አልሚ አርሶ አደሮች ከ4 ሺህ በላይ የውሃ መሳቢያ ሞተሮችን ጨምሮ ከ50 ሺህ ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያና ምርጥ ዘር በማቅረብ ለመስኖ ልማቱ ድጋፍ መደረጉን አስረድተዋል፡፡
በዞኑ የተገነቡ አነስተኛ፣ መካከለኛና ከፍተኛ የመስኖ አውታሮችም አርሶ አደሩ ከዝናብ ጥገኝነት ተላቆ በዓመት እስከ ሶስት ጊዜ ማምረት የሚችልበትን እድል ፈጥረዋል ነው ያሉት።

አንደኛው ዙር የመስኖ ልማት ተጠናቆ ሁለተኛው ዙር መጀመሩን ጠቁመው በአሁኑ ወቅትም፤ ከ10 ሺህ ሔክታር በላይ መሬት በመስኖ እየለማ እንደሚገኝ አመልክተዋል፡፡
ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...
Aug 28, 2026
መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...
Aug 18, 2026
ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...
Aug 10, 2026
አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...
Jul 20, 2026