የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

መንግሥት የዜጎችን የኑሮ ጫና ለመቀነስ በርካታ ቢሊዮን ብሮችን በመመደብ እና አመራጮችን ሁሉ አሟጦ በመጠቀም የነዳጅ አቅርቦትን አስቀጥሏል

Apr 29, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ መንግሥት የዜጎችን የኑሮ ጫና ለመቀነስ በርካታ ቢሊዮን ብሮችን በመመደብ እና አማራጮችን ሁሉ አሟጦ በመጠቀም የነዳጅ አቅርቦትን ማስቀጠሉን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ።

መንግሥት በመሠረታዊ ፍላጎቶቿ በራሷ የምታሟላ ሉዓላዊ ሀገር ለመፍጠር ፖሊሲ ቀርጾ እየሠራ ይገኛል። በተለይም ከነዳጅ ጥገኝነት ለመላቀቅ ቀድሞ ወደ ሥራ መግባቱ፣ በሀገር ላይ ይደርስ የነበረን የከፋ ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ከሌሎች ሀገራት አንጻር በከፍተኛ ደረጃ ማስቀረት እንደቻለ ገልጿል።

ምንም እንኳ ሙሉ ለሙሉ ከነዳጅ ጥገኝነት ለመላቀቅ ገና ሰፊ የመንግሥት እና የግሉ ዘርፍ ጥረት ቢጠይቅም፣ ባለፉት ስምንት ዓመታት በታዳሽ የኃይል ዘርፍ አቅርቦት ላይ የተሠራው ሥራ አሁን ያለውን ቀውስ ለመቋቋም በእጅጉ ማገዙን አመልክቷል።

የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ሙሉ በሙሉ ከታዳሽ የኃይል ምንጮች ማለትም ከውኃ፣ ከነፋስ እና ከፀሐይ የሚገኝ ሲሆን፤ በቀጣይም ከጂኦተርማል እና ከኑክሊየር ኃይል በማመንጨት የሀገሪቱን ፍላጎት በአስተማማኝ ደረጃ ለማሟላት እየተሠራ ይገኛልም ነው ያለው አገልግሎቱ።

የኃይል ምንጮችን ታዳሽ ማድረግ መቻሉ፣ አሁን ካጋጠመው ዓለም አቀፍ የነዳጅ እጥረትና የዋጋ መናር ጋር ተያይዞ በሀገሪቱ አምራች ኢንዱስትሪዎች ላይ ሊከሰት ይችል የነበረን ጫና ማስቀረት ማስቻሉን ገልጿል።

መንግሥት ላለፉት ዓመታት ዜጎች የታዳሽ ኃይል አማራጮችን እንዲጠቀሙ የተለያዩ የማበረታቻ ሥርዓቶችን ተግባራዊ አድርጓል።

በዚህም የመንግሥትን አቅጣጫ በመቀበል የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን መጠቀም የጀመሩ ዜጎች አሁን ላይ የችግሩ ሰለባ አለመሆናቸውን መረጃው አመላክቷል።

ይህም ለዘገዩት ትምህርት የሚሰጥ ሲሆን፣ ለመንግሥት ደግሞ ለሚከተለው የፖሊሲ አቅጣጫ ትክክለኛነት በራስ መተማመን የሚፈጥር እንደሆነም ተነስቷል።

በአሁኑ ወቅት ከ140 ሺህ ያላነሱ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች የሚገኙ ሲሆን፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ ይህንን መጠን በብዙ እጥፍ ለማሳደግ ታቅዶ እየተሠራ መሆኑን አገልግሎቱ ጠቁሟል።

መንግሥት የኃይል ሉዓላዊነትን በታዳሽ የኃይል ምንጮች ላይ ተመሥርቶ ለማረጋገጥ ጥረት እያደረገ ነው።

የታላቁ ሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅ የኢትዮጵያን የኃይል አቅርቦት በከፍተኛ ደረጃ ሲያሳድገው፣ የነፋስ ኃይል ማመንጫዎችም በየጊዜው እየተመረቁ ወደ ሥራ እየገቡ ይገኛሉ። በአፍሪካ ግዙፍ የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ሶላር ፓኔሎችን የማምረት አቅም የተፈጠረ ሲሆን፣ የግሉ ዘርፍ ተሳትፎም እየተበረታታ እንደሚገኝም ተነስቷል።

በተጨማሪም የነዳጅ ማጣሪያ እና የተፈጥሮ ጋዝ ማምረቻ ፋብሪካዎች ግንባታ እየተፋጠነ መሆኑ ተጠቁሟል።

በእነዚህ ሁሉ ጥረቶች መካከል አሁን ያጋጠመው ዓለም አቀፍ ቀውስ በዜጎች ላይ የከፋ ጉዳት እንዳያደርስ ለመከላከል፣ መንግሥት ቀደም ሲል ሲደጉም ከነበረው በተጨማሪ በየወሩ 20 ቢሊዮን ብር በመደጎም እና የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም የነዳጅ አቅርቦትን እያስቀጠለ እንደሚገኝ አገልግሎቱ አስታውቋል።

መንግሥት በአረንጓዴ የኢኮኖሚ ፖሊሲ አቅጣጫ አማካኝነት ችግሩን በዘላቂነት ከሕዝቡ ጋር እንደሚሻገረው እና የመውጫ በሩም ከቅርብ ርቀት ይታያል ሲል አገልግሎቱ በመረጃው አመላክቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሚያዝያ እና ግንቦት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት ከምስል ጋር!

  የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...

Jun 4, 2026

በዲጂታል ክህሎት ራሳችንን እያበቃን ነው - ተማሪዎች

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...

Jun 1, 2026

በኦሮሚያ ክልል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ የአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት ተሰጥቷል

አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...

May 25, 2026

በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው

ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...

May 15, 2026