የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

መንግሥት የዜጎችን የኑሮ ጫና ለመቀነስ በርካታ ቢሊዮን ብሮችን በመመደብ እና አመራጮችን ሁሉ አሟጦ በመጠቀም የነዳጅ አቅርቦትን አስቀጥሏል

Apr 29, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ መንግሥት የዜጎችን የኑሮ ጫና ለመቀነስ በርካታ ቢሊዮን ብሮችን በመመደብ እና አማራጮችን ሁሉ አሟጦ በመጠቀም የነዳጅ አቅርቦትን ማስቀጠሉን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ።

መንግሥት በመሠረታዊ ፍላጎቶቿ በራሷ የምታሟላ ሉዓላዊ ሀገር ለመፍጠር ፖሊሲ ቀርጾ እየሠራ ይገኛል። በተለይም ከነዳጅ ጥገኝነት ለመላቀቅ ቀድሞ ወደ ሥራ መግባቱ፣ በሀገር ላይ ይደርስ የነበረን የከፋ ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ከሌሎች ሀገራት አንጻር በከፍተኛ ደረጃ ማስቀረት እንደቻለ ገልጿል።

ምንም እንኳ ሙሉ ለሙሉ ከነዳጅ ጥገኝነት ለመላቀቅ ገና ሰፊ የመንግሥት እና የግሉ ዘርፍ ጥረት ቢጠይቅም፣ ባለፉት ስምንት ዓመታት በታዳሽ የኃይል ዘርፍ አቅርቦት ላይ የተሠራው ሥራ አሁን ያለውን ቀውስ ለመቋቋም በእጅጉ ማገዙን አመልክቷል።

የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ሙሉ በሙሉ ከታዳሽ የኃይል ምንጮች ማለትም ከውኃ፣ ከነፋስ እና ከፀሐይ የሚገኝ ሲሆን፤ በቀጣይም ከጂኦተርማል እና ከኑክሊየር ኃይል በማመንጨት የሀገሪቱን ፍላጎት በአስተማማኝ ደረጃ ለማሟላት እየተሠራ ይገኛልም ነው ያለው አገልግሎቱ።

የኃይል ምንጮችን ታዳሽ ማድረግ መቻሉ፣ አሁን ካጋጠመው ዓለም አቀፍ የነዳጅ እጥረትና የዋጋ መናር ጋር ተያይዞ በሀገሪቱ አምራች ኢንዱስትሪዎች ላይ ሊከሰት ይችል የነበረን ጫና ማስቀረት ማስቻሉን ገልጿል።

መንግሥት ላለፉት ዓመታት ዜጎች የታዳሽ ኃይል አማራጮችን እንዲጠቀሙ የተለያዩ የማበረታቻ ሥርዓቶችን ተግባራዊ አድርጓል።

በዚህም የመንግሥትን አቅጣጫ በመቀበል የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን መጠቀም የጀመሩ ዜጎች አሁን ላይ የችግሩ ሰለባ አለመሆናቸውን መረጃው አመላክቷል።

ይህም ለዘገዩት ትምህርት የሚሰጥ ሲሆን፣ ለመንግሥት ደግሞ ለሚከተለው የፖሊሲ አቅጣጫ ትክክለኛነት በራስ መተማመን የሚፈጥር እንደሆነም ተነስቷል።

በአሁኑ ወቅት ከ140 ሺህ ያላነሱ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች የሚገኙ ሲሆን፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ ይህንን መጠን በብዙ እጥፍ ለማሳደግ ታቅዶ እየተሠራ መሆኑን አገልግሎቱ ጠቁሟል።

መንግሥት የኃይል ሉዓላዊነትን በታዳሽ የኃይል ምንጮች ላይ ተመሥርቶ ለማረጋገጥ ጥረት እያደረገ ነው።

የታላቁ ሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅ የኢትዮጵያን የኃይል አቅርቦት በከፍተኛ ደረጃ ሲያሳድገው፣ የነፋስ ኃይል ማመንጫዎችም በየጊዜው እየተመረቁ ወደ ሥራ እየገቡ ይገኛሉ። በአፍሪካ ግዙፍ የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ሶላር ፓኔሎችን የማምረት አቅም የተፈጠረ ሲሆን፣ የግሉ ዘርፍ ተሳትፎም እየተበረታታ እንደሚገኝም ተነስቷል።

በተጨማሪም የነዳጅ ማጣሪያ እና የተፈጥሮ ጋዝ ማምረቻ ፋብሪካዎች ግንባታ እየተፋጠነ መሆኑ ተጠቁሟል።

በእነዚህ ሁሉ ጥረቶች መካከል አሁን ያጋጠመው ዓለም አቀፍ ቀውስ በዜጎች ላይ የከፋ ጉዳት እንዳያደርስ ለመከላከል፣ መንግሥት ቀደም ሲል ሲደጉም ከነበረው በተጨማሪ በየወሩ 20 ቢሊዮን ብር በመደጎም እና የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም የነዳጅ አቅርቦትን እያስቀጠለ እንደሚገኝ አገልግሎቱ አስታውቋል።

መንግሥት በአረንጓዴ የኢኮኖሚ ፖሊሲ አቅጣጫ አማካኝነት ችግሩን በዘላቂነት ከሕዝቡ ጋር እንደሚሻገረው እና የመውጫ በሩም ከቅርብ ርቀት ይታያል ሲል አገልግሎቱ በመረጃው አመላክቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026