የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በኢትዮጵያ በሰው ሰራሽ አስተውሎት ዘርፍ የተመዘገቡ ስኬቶች ለአህጉራዊ መሪነት መሰረት ሆነዋል

May 6, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 23/2018 (ኢዜአ)፦በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት በሰው ሰራሽ አስተውሎት የተመዘገቡ ስኬቶች ለኢትዮጵያ የዘርፉ አህጉራዊ መሪነት መሰረት መሆናቸውን የፌዴራል ሕግና ፍትህ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ደግፌ ቡላ ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአፍሪካ ኅብረት የሰው ሰራሽ አስተውሎት እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ (Champion) ሆነው ተሹመዋል።

ሹመቱ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዘርፉ ላሳዩት አመራርና ኢትዮጵያ በአህጉሪቱ የሰው ሰራሽ አስተውሎትንና የፈጠራ ሥራዎችን ለማስፋፋት እየተገበረች ላለው የላቀ ሚና የተሰጠ እውቅና መሆኑ ተገልጿል።

ኢትዮጵያ ሰው ሰራሽ አስተውሎትን ሥነ-ምግባራዊ መርሆች በተከተለ መልኩ በማልማት፣ በመመራመር እንዲሁም ተግባራዊ በማድረግ በኩል ከአፍሪካ ቀዳሚዋ ሀገር እንድትሆን ለተሠሩ ሥራዎች እውቅና የሰጠ ነው ተብሏል።

የፌዴራል ሕግና ፍትህ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ደግፌ ቡላ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ ኢትዮጵያ የአሠራር ሥርዓቷን ዲጂታል ለማድረግ እያከናወነች ያለችው ስራ በከፍተኛ የዕድገት ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡

እንዲሁም ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራትም እንደ ትልቅ ተሞክሮ ሊወሰድ የሚችል መሆኑን ገልፀዋል።

ለዚህም ማሳያ እንዲሆን በስኬት የተጠናቀቀውን 'ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025' ስትራቴጂ እና በአሁኑ ወቅት ተግባራዊ እየተደረገ የሚገኘውን 'ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030' ስትራቴጂን በአብነት ጠቅሰዋል።

በተለይም በመንግሥት ተቋማት ውስጥ የአሰራር ቅልጥፍናን ለማምጣት እየተተገበረ ያለው የዲጂታል መንግሥታዊ አሠራር (e-government) ሥርዓት፣ ተጨባጭ ውጤት እያመጣ መሆኑን አስረድተዋል።

ይህም ለዜጎች የሚሰጡ አገልግሎቶችን ለማዘመንና ተደራሽ ለማድረግ ጉልህ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝ አስገንዝበዋል።

ኢትዮጵያ በሰው ሰራሽ አስተውሎት ዘርፍ እያከናወነች ያሉ ውጤታማ ሥራዎች እውቅና እያገኙ መምጣታቸውን ጠቅሰዋል፡፡

ለዚህም በቅርቡ የአፍሪካ ህብረት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዘርፉን በአህጉር ደረጃ እንዲመሩ የሰጠው ሹመት የኢትዮጵያን ስኬትና አርዓያነት የሚያሳይ ነው ብለዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዘርፉ ያላቸውን ጥልቅ እውቀትና የዳበረ ልምድ መሠረት በማድረግ፣ ኢትዮጵያ በዲጂታል ዘርፍ ውጤታማ እንድትሆንና የለውጥ እርምጃዎችን እንድታፋጥን ቁልፍ የአመራርነት ሚና እየተጫወቱ እንደሚገኙ አስረድተዋል።

የዲጂታል ሥርዓት ግንባታ የሀገሪቱን ተጠቃሚነት ከማረጋገጥ ባለፈ፣ ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራትም አርዓያ የሚሆንና አህጉራዊ የጋራ ብልጽግናን ለማምጣት ተስፋ የሚሰጥ መሆኑን አብራርተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሚያዝያ እና ግንቦት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት ከምስል ጋር!

  የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...

Jun 4, 2026

በዲጂታል ክህሎት ራሳችንን እያበቃን ነው - ተማሪዎች

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...

Jun 1, 2026

በኦሮሚያ ክልል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ የአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት ተሰጥቷል

አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...

May 25, 2026

በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው

ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...

May 15, 2026