🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 7/2018 (ኢዜአ)፦ዓለም አቀፍ ስታንዳርድ የጠበቀ የሚቲዎሮሎጂ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችሉ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን ሥራ ላይ በማዋል ተጨባጭ ውጤቶች እየተገኙ መሆኑን የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ።
የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር እና የዓለም ሚቲዎሮሎጂ ድርጅት የአፍሪካ አህጉር ፕሬዚዳንት አቶ ፈጠነ ተሾመ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የኢንስቲትዩቱ የትንበያ አቅም በሰው ኃይል፣ በቴክኖሎጂ መሠረተ ልማት ዝርጋታና በተደራሽነት ረገድ ወደ ላቀ ደረጃ እየተሸጋገረ ይገኛል።
በአሁኑ ወቅትም የአጭር፣ የመካከለኛና የረጅም ጊዜ የአየር ሁኔታ ትንበያዎችን ለውሳኔ ሰጪ አካላትና ለተጠቃሚው ማኅበረሰብ በወቅቱ ተደራሽ እያደረገ መሆኑንም ገልጸዋል።
ኢንስቲትዩቱ ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የሚቲዎሮሎጂ አገልግሎት ለመስጠት ካስቀመጠው ግብ አንጻር፣ ግቡን ለማሳካት የሚያስችሉ ሁለንተናዊ የሚቲዎሮሎጂ ምልከታ መሠረተ ልማቶች በአገር አቀፍ ደረጃ መዘርጋታቸውን ጠቁመዋል።

የአየር ሁኔታን በቅርበት ለመከታተል የሚያስችሉ ዘመናዊ ራዳሮች በአራት ስትራቴጂካዊ የአገሪቱ አካባቢዎች ላይ ተተክለው በቅርቡ ወደ ሥራ መግባታቸውን ጠቁመዋል፡፡
ራዳሮቹ የተተከሉባቸው ቀጠናዎች በሰሜን ምዕራብ ኢትዮጵያ፣ በምዕራብ ኢትዮጵያ፣ በመካከለኛው ኢትዮጵያ እና በደቡብ ኢትዮጵያ መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡
እነዚህ ዘመናዊ ራዳሮች በተተከሉበት ስፍራ ዙሪያ እስከ 250 ኪሎ ሜትር ክብ ርቀት (ራዲየስ) ውስጥ ያለውን ማንኛውንም የሚቲዎሮሎጂ ለውጥና መረጃ በቀጥታ ወደ ማዕከላዊ የመረጃ ቋት የመላክ ከፍተኛ አቅም እንዳላቸው አብራርተዋል።
ከራዳር ዝርጋታው በተጨማሪ፣ የአየር ንብረት መረጃዎችን በከፍተኛ ፍጥነት ወደ መረጃ ቋት የመላክ አቅም ያላቸው የ‘አውቶማቲክ ዌዘር ስቴሽኖች’ ተከላ እየተካሄደ መሆኑን አንስተዋል።

እነዚህ ወደ ሥራ የገቡና እየተዘረጉ ያሉ ቴክኖሎጂዎች ዓለም የደረሰበትን ከፍተኛ የሚቲዎሮሎጂ ምልከታ ደረጃ የጠበቁ መሆናቸውን ጠቅሰው፤ በዚህም የአገሪቱን የትንበያና የቅድመ ማስጠንቀቂያ አቅም በማጎልበት ረገድ የሚጫወቱት ሚና ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል።
ቴክኖሎጂዎቹ ተደራሽነትን ከማስፋታቸውም በላይ ማኅበረሰቡ ወቅቱን የጠበቀና አስተማማኝ አገልግሎት እንዲያገኝ እንደሚያስችሉ አስገንዝበዋል።
የቴክኖሎጂ ውጤቶቹ ለግብርናው ክፍለ ኢኮኖሚ፣ በአየር ንብረት ለውጥ ሳቢያ ሊከሰት የሚችለውን ጉዳት በቅድመ ማስጠንቀቂያ ለመቀነስ ብሎም ለሌሎች መሠረታዊ ጉዳየች ያላቸው ፋይዳ የጎላ ነው፡፡
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026