የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የሚቲዎሮሎጂ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችሉ ቴክኖሎጂዎችን ሥራ ላይ በማዋል ተጨባጭ ውጤቶች እየተገኙ ነው

May 15, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 7/2018 (ኢዜአ)፦ዓለም አቀፍ ስታንዳርድ የጠበቀ የሚቲዎሮሎጂ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችሉ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን ሥራ ላይ በማዋል ተጨባጭ ውጤቶች እየተገኙ መሆኑን የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ።

የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር እና የዓለም ሚቲዎሮሎጂ ድርጅት የአፍሪካ አህጉር ፕሬዚዳንት አቶ ፈጠነ ተሾመ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የኢንስቲትዩቱ የትንበያ አቅም በሰው ኃይል፣ በቴክኖሎጂ መሠረተ ልማት ዝርጋታና በተደራሽነት ረገድ ወደ ላቀ ደረጃ እየተሸጋገረ ይገኛል።

በአሁኑ ወቅትም የአጭር፣ የመካከለኛና የረጅም ጊዜ የአየር ሁኔታ ትንበያዎችን ለውሳኔ ሰጪ አካላትና ለተጠቃሚው ማኅበረሰብ በወቅቱ ተደራሽ እያደረገ መሆኑንም ገልጸዋል።

ኢንስቲትዩቱ ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የሚቲዎሮሎጂ አገልግሎት ለመስጠት ካስቀመጠው ግብ አንጻር፣ ግቡን ለማሳካት የሚያስችሉ ሁለንተናዊ የሚቲዎሮሎጂ ምልከታ መሠረተ ልማቶች በአገር አቀፍ ደረጃ መዘርጋታቸውን ጠቁመዋል።


የአየር ሁኔታን በቅርበት ለመከታተል የሚያስችሉ ዘመናዊ ራዳሮች በአራት ስትራቴጂካዊ የአገሪቱ አካባቢዎች ላይ ተተክለው በቅርቡ ወደ ሥራ መግባታቸውን ጠቁመዋል፡፡

ራዳሮቹ የተተከሉባቸው ቀጠናዎች በሰሜን ምዕራብ ኢትዮጵያ፣ በምዕራብ ኢትዮጵያ፣ በመካከለኛው ኢትዮጵያ እና በደቡብ ኢትዮጵያ መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡

እነዚህ ዘመናዊ ራዳሮች በተተከሉበት ስፍራ ዙሪያ እስከ 250 ኪሎ ሜትር ክብ ርቀት (ራዲየስ) ውስጥ ያለውን ማንኛውንም የሚቲዎሮሎጂ ለውጥና መረጃ በቀጥታ ወደ ማዕከላዊ የመረጃ ቋት የመላክ ከፍተኛ አቅም እንዳላቸው አብራርተዋል።

ከራዳር ዝርጋታው በተጨማሪ፣ የአየር ንብረት መረጃዎችን በከፍተኛ ፍጥነት ወደ መረጃ ቋት የመላክ አቅም ያላቸው የ‘አውቶማቲክ ዌዘር ስቴሽኖች’ ተከላ እየተካሄደ መሆኑን አንስተዋል።


እነዚህ ወደ ሥራ የገቡና እየተዘረጉ ያሉ ቴክኖሎጂዎች ዓለም የደረሰበትን ከፍተኛ የሚቲዎሮሎጂ ምልከታ ደረጃ የጠበቁ መሆናቸውን ጠቅሰው፤ በዚህም የአገሪቱን የትንበያና የቅድመ ማስጠንቀቂያ አቅም በማጎልበት ረገድ የሚጫወቱት ሚና ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል።

ቴክኖሎጂዎቹ ተደራሽነትን ከማስፋታቸውም በላይ ማኅበረሰቡ ወቅቱን የጠበቀና አስተማማኝ አገልግሎት እንዲያገኝ እንደሚያስችሉ አስገንዝበዋል።

የቴክኖሎጂ ውጤቶቹ ለግብርናው ክፍለ ኢኮኖሚ፣ በአየር ንብረት ለውጥ ሳቢያ ሊከሰት የሚችለውን ጉዳት በቅድመ ማስጠንቀቂያ ለመቀነስ ብሎም ለሌሎች መሠረታዊ ጉዳየች ያላቸው ፋይዳ የጎላ ነው፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026