የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪና ጠንካራ የአእምሯዊ ንብረት ጥበቃ ሥርዓት መገንባት የሚያስችል አቅም እየተፈጠረ ነው

May 28, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 18/2018(ኢዜአ)፦ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪና ጠንካራ የአእምሯዊ ንብረት ጥበቃ ሥርዓት መገንባት የሚያስችል አቅም እየተፈጠረ መሆኑን የኢትዮጵያ አእምሯዊ ንብረት ባለስልጣን ገለጸ።

የአእምሯዊ ንብረት ዘርፍ ዓለም አቀፋዊ ሁኔታዎችን ከሀገራዊ የአእምሯዊ ንብረት ምዝገባና ጥበቃ ጋር ማቀናጀት ላይ ያተኮረ የባለድርሻ አካላት ውይይት ተካሂዷል።


የኢትዮጵያ አእምሯዊ ንብረት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወልዱ ይመስል፤ በዓለም አቀፍ ደረጃ የግዙፍ ኩባንያዎች ሃብት ከፍተኛው ድርሻ ወደ አእምሯዊ ንብረት እየተቀየረ ነው ብለዋል።

በኢትዮጵያም የአእምሯዊ ንብረት ለኢኮኖሚ ዕድገት የሚያበረክተውን አስተዋጽኦ ለማሳደግ የፖሊሲ፣ የሕግና የዲጂታል የአእምሯዊ ንብረት አስተዳደር ሥርዓት እየተዘረጋ መሆኑን ገልጸዋል።

የአእምሯዊ ንብረት ምዝገባ ሥርዓቱን በአስቻይ የአሰራር ምኅዳር ለሀገር የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ የራሱን ድርሻ እንዲወጣ እየተሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

ከሀገር ውስጥና ዓለምአቀፍ ሕግና ስምምነቶች ጋር የተጣጣመ የአእምሯዊ ንብረት ጥበቃ ለውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት፣ ለጥናትና ምርምር ሥራ መሳለጥ ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለውም አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ አእምሯዊ ንብረት ጥበቃ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነትና የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ስምምነት የንግድና ፈጠራ ተወዳዳሪነትን ለማሳደግ አይነተኛ ሚና እንደሚኖረው አንስተዋል።


የአእምሯዊ ንብረት ዘርፍ የሕግ አማካሪ ኤልያስ ፍቅሩ፤ የአእምሯዊ ንብረት ጥበቃ ዓለምአቀፍ ፈጠራና ኢንቨስትመንትን በማበረታታት ወሳኝ ፋይዳ አለው ብለዋል።

የኢትዮጵያ አእምሯዊ ንብረት ጥበቃ ሥርዓት መጠናከር ፈጠራና ኢንቨስትመንትን በማበረታታት ዓለምአቀፍ ተወዳዳሪነትን ማሳደግ እንደሚያስችል ገልጸዋል።


በኢትዮጵያ የቅጂና ተዛማች መብቶች የጋራ አስተዳደር ማኅበር የቦርድ አባል አርቲስት ጸደንያ ገብረማርቆስ፤ የአእምሯዊ ንብረት ጥበቃ የሚደረግላቸው ምርቶች ለኢኮኖሚ ዕድገት ጉልህ ፋይዳ አላቸው ብላለች።

ለዚህም የኪነ-ጥበብ ሥራ ቅጂና ተዛማጅ የሕግ ግንዛቤን በማጎልበት ጠንካራ የአእምሯዊ ንብረት ጥበቃ አቅም መገንባት እንደሚያስፈልግ ተናግራለች።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሚያዝያ እና ግንቦት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት ከምስል ጋር!

  የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...

Jun 4, 2026

በዲጂታል ክህሎት ራሳችንን እያበቃን ነው - ተማሪዎች

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...

Jun 1, 2026

በኦሮሚያ ክልል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ የአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት ተሰጥቷል

አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...

May 25, 2026

በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው

ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...

May 15, 2026