🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 18/2018(ኢዜአ)፦ የቅዳሜና እሁድ ገበያዎች በየአካባቢው መስፋፋታቸው የተለያዩ የግብርና ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ እንድናገኝ አስችሎናል ሲሉ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ገለጹ።
የቅዳሜና እሁድ ገበያዎች በተለያዩ አካባቢዎች ላይ ሕብረተሰቡ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያገኙ በማድረግና ገበያን በማረጋጋት በኩል ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከቱ መሆኑ ይታወቃል።
በዚህም የተለያዩ የግብርና ምርቶችን ጨምሮ የተለያዩ ሸቀጦች በተመጣጣኝ ዋጋ እየቀረቡ ይገኛሉ።
በጉዳዩ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው አስተያየት ሰጪዎች እንደገለጹት፤ የቅዳሜና እሁድ ገበያዎች በአቅራቢያችን በመጀመሩ የግብይት ስርዓቱን ቀልጣፋ እና ምቹ አድርጎታል።

አስተያየት ከሰጡ ሸማቾች መካከል ወይዘሮ ገነት አድማሱ፤ ገበያው በአቅራቢያችን በመከፈቱ የፍጆታ እቃዎችን በቀላሉ በተመጣጣኝ ዋጋ ማግኘት አስችሎናል ብለዋል።
ይህ አይነት ገበያ መኖሩ ለነዋሪዎች ምቹና ቀልጣፋ አገልግሎትን ከማግኘት ባለፈ የዋጋ ንረትን ለማረጋጋት ትልቅ አስታዋጽኦ እንዳለው ተናግረዋል።

ወይዘሮ ጸጋ አዱሽ በበኩላቸው፤ በቅዳሜ እና እሁድ ገበያዎች የአትክልትና ፍራፍሬ በብዛት ከመቅረቡ ባሻገር ሰፊ አማራጮች የሚገኙበት ነው ብለዋል።
የቅዳሜና እሁድ ገበያዎች በየአካባቢው መኖሩ ለአቅመ ደካሞችና ረጅም መንገድ ተጉዘው መገበያየት ለማይችሉ ትልቅ ጥቅም እንዳለው ገልጸው፤ ገበያው ላይ በተመጣጣኝ ዋጋ እንደሚያገኝ የገለጸችው ደግሞ ማአዛነሽ መለሰ ናቸው።

በቅዳሜ እሁድ ገበያዎች ምርቶቻቸውን ይዘው የቀረቡ ነጋዴዎች በበኩላቸው፤ ጥራቱን የጠበቀ ምርት በተመጣጣኝ ዋጋ ለገበያ እያቀረቡ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
አስተያየታቸውን ካጋሩን መካከል እየሩሳሌም ሐብቶም፤ የቅዳሜና እሁድ ገበያዎች በበርካታ የህብረተሰብ ክፍሎች ነዋሪዎች ተፈላጊነቱ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መጥቷል ብለዋል።

ይህን ፍላጎት ለማሟላት ጥራት ያላቸውን ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ ለሸማቹ እያቀረቡ መሆኑን ነው የሚናገሩት።

ሌላኛዋ ነጋዴ ቤተልሔም አዱኛ የቅዳሜና እሁድ ገበያዎች የዋጋ ንረትን በመቀነስ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማስፋት መጀመሩን ገልጸው፤ ከመደበኛ ሱቆች ከፍተኛ ልዩነት እንዳለው ጠቁመዋል።
በአዲስ አበባ ሸማቾች በቀላሉ በአቅራቢያቸው መገብየት የሚያስችሉ በሁሉም አካባቢዎች 250 የቅዳሜና እሁድ ገበያዎች አሉ።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026