የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የኢንዱስትሪ ፓርኩ መገንባት መንግሥት ለዘርፉ የሰጠውን ትኩረት በተጨባጭ ያረጋገጠ ነው

May 20, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና በስትራቴጂ ከመደገፍ ባለፈ በተጨባጭ ያለውን ቁርጠኝነት ያሳየበት መሆኑን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል ገለጹ።

የኢንዱስትሪ ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል ባሳለፍነው ሳምንት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተመርቆ የተከፈተውን የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክን ጎብኝተዋል።


ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል በዚሁ ጊዜ እንደተናገሩት፤ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት፤ መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና በስትራቴጂ ከመደገፍ ባለፈ በተጨባጭ ያለውን ቁርጠኝነት ያሳየበት ነው።

ፓርኩ በአምራች ዘርፉ ላይ የሚስተዋለውን የመሥሪያ ቦታ እጥረት በዘላቂነት ለመፍታት የማይተካካ ሚና አለው ብለዋል።

አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች አቅማቸውን ገንብተው ወደ ከፍተኛ ኢንዱስትሪነት እንዲሸጋገሩ ምቹ ሁኔታን እንደሚፈጥር ተናግረዋል።

ፓርኩ የተገነባበት ጥራትና የተሟላ መሠረተ ልማት የሀገር ውስጥ ምርትን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ለማድረግ ያስችላል ሲሉ ገልፀዋል።


የሀገር ውስጥ ምርትን በማሳደግ የገቢ ምርቶችን ለመተካት የሚደረገውን ጥረት ለሀገር ዘላቂ ሉዓላዊነት ትልቅ አስተዋፅኦ ይኖረዋል ብለዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እንዲህ አይነት ግዙፍ ፕሮጀክት መገንባቱ ትልቅ ልምድና ትምህርት የተገኘበት መሆኑን ጠቅሰው፤ ለሌሎች አካባቢዎችም እንደ ማዕከልና አርዓያ ሆኖ እንደሚያገለግል አስገንዝበዋል።

በሁሉም አካባቢዎች ኢንዱስትሪን ለማስፋፋትና የሀገርን ተወዳዳሪነት ለማሳደግ ጉልህ ሚና ይጫወታል ብለዋል።


የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ታረቀኝ ቡሉልታ በበኩላቸው፤ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጀመረውን የኢንዱስትሪ ንቅናቄን እንደሚያግዝ ገልጸው፤ ይህም የሀገር ውስጥ የገበያ ድርሻን በማሳደግ ለኢንዱስትሪዎች ጠንካራ መሠረት የሚጥል ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026

በሲዳማ ክልል የሆኮ ወረዳ ነዋሪዎች በአማራጭ የኃይል አቅርቦት ሥራዎች ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ፤ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ):-በሲዳማ ክልል የሆኮ ወረዳ ነዋሪዎች በመንግስት በተከናወኑ አማራጭ የኃይል አቅርቦት ሥራዎች ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናገሩ። ...

Jun 25, 2026

የኢንዱስትሪ ፓርኩ መገንባት መንግሥት ለዘርፉ የሰጠውን ትኩረት በተጨባጭ ያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...

May 20, 2026