የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በበጀት ዓመቱ ከ5 ሚሊዮን ለሚበልጡ ዜጎች የሥራ ዕድል ተፈጥሯል

Jul 14, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

‎ሀዋሳ፤ ሐምሌ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ5 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፈጠሩን የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ገለፀ።

‎የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የሥራ ዕድል ፈጠራ ዘርፍ የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዓመት የትኩረት አቅጣጫን አስመልክቶ በሀዋሳ ከተማ ዛሬ የውይይት መድረክ አካሂዷል።


በመድረኩ ላይ በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የሥራ፣ የሥራ ስምሪትና ገበያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ እንዳሉት፣ በበጀት ዓመቱ በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገር የሥራ ሥምሪት 5 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዜጎች የሥራ ዕድል ተፈጥሯል።

በሀገር ውስጥ የሥራ ስምሪት በግብርና፣ በኢንዱስትሪና በአገልግሎት ዘርፍ ከ4 ነጥብ 9 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የሥራ ዕድል የተፈጠረላቸው ሲሆን ከ670 ሺህ በላይ ዜጎች ደግሞ በውጭ ሀገር የሥራ ዕድል ማግኘታቸውን ገልጸዋል።

ለኢንተርፕራይዞች በፋይናንስ አቅርቦት ላይ ያለውን ክፍተት ለመሙላት ከባንኮችና ጋር በቅንጅት በመሰራቱ በበጀት ዓመቱ 85 ቢሊዮን ብር የሚጠጋ የገንዘብ ብድር ለማቅረብ እንደተቻለም ተናግረዋል፡፡

እንደ አቶ ሰለሞን ገለጻ፣ የሥራ ዕድል ፈጠራን ለማስፋትም የቤተሰብና የማህበረሰብ ሀብቶችን ለሥራ ዕድል ፈጠራ ለማዋል በቁርጠኝነት ተሰርቷል።

ለሥራ ዕድል ፈጠራው ስኬትም ኢንተርፕራይዞችን የመደገፍ ፣ አዳዲስ የፈጠራ ሀሳቦችን የማበረታታትና ዲጂታል የሥራ መስኮችን የማስፋት ሥራ ትኩረት እንደተሰጠውም አስረድተዋል፡፡


በመድረኩ ላይ የተገኙት የኦሮሚያ ክልል ሥራ ዕድል ፈጠራና ክህሎት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ዋሲሁን ጎልጋ በበኩላቸው፣ በክልሉ ያለውን የሥራ አቅም የመለየትና የሰው ኃይል ብቃት ላይ መሰራቱን ጠቅሰዋል፡፡

በዚህም በበጀት ዓመቱ ለ5 ነጥብ 8 ሚሊዮን ዜጎች የሥራ ፈጠራ ሥልጠናዎች መሰጠቱን አስረድተዋል፡፡

የሲዳማ ክልል ሥራ፣ ክህሎትና ኢንተርፕራይዝ ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ከፍያለው ከበደ በክልሉ የሥራ መስኮችን በማስፋት ስኬታማ ሥራዎች መከናወናቸውን ጠቅሰዋል።


ከባለድርሻ አካላት እና ከአጋር ድርጅቶች ጋር ተቀናጅቶ በመስራት የማምረቻና የመሸጫ ቦታ ችግር በመፍታት ለዜጎች የሥራ ዕድል ለመፍጠር መቻሉንም ጠቁመዋል፡፡

በመድረኩ የፌዴራል እንዲሁም የክልልና የከተማ አስተዳደሮች የዘርፉ ከፍተኛ አመራር አካላት ተገኝተዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026

በሲዳማ ክልል የሆኮ ወረዳ ነዋሪዎች በአማራጭ የኃይል አቅርቦት ሥራዎች ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ፤ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ):-በሲዳማ ክልል የሆኮ ወረዳ ነዋሪዎች በመንግስት በተከናወኑ አማራጭ የኃይል አቅርቦት ሥራዎች ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናገሩ። ...

Jun 25, 2026

የኢንዱስትሪ ፓርኩ መገንባት መንግሥት ለዘርፉ የሰጠውን ትኩረት በተጨባጭ ያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...

May 20, 2026