የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

<p>ኢንስቲትዩቱ እርጎን ከ10 ቀናት በላይ ሳይበላሽ ማቆየት የሚያስችል እርሾ አመረተ</p>

Feb 6, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ጥር 19/2017(ኢዜአ)፦ የባዮ እና ኢመርንጂንግ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ወተትን በሰዓታት ውስጥ ማርጋትና እርጎን ከ10 ቀናት በላይ ሳይበላሽ ማቆየት የሚያስችል እርሾ ማምረቱን ይፋ አደረገ፡፡

ከፍተኛ የቁም እንስሳት ሀብት ባላት ኢትዮጵያ ወተትን በነፍስ ወከፍ የመጠቀም ምጣኔ በዓመት ከ19 ሊትር አይበልጥም።

በዚህም መንግስት የወተት ኃብት ልማት ስትራቴጂ ነድፎ የሌማት ትሩፋትን ጨምሮ የወተት ምርታማነትንና የነፍስ ወከፍ ፍጆታን ለማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን በትኩረት እየሰራ ነው።

የወተት ልማቱን ማሳደግ፣ የወተት ምርት ላይ እሴቶችን መጨመር እና የምርት ጥራትና ደኅንነት ማስጠበቅ ላይ ትኩረት ተሰጥቷል።

በዘርፉ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማስፋት የተቀመጠውን ግብ ለማሳካት ከተቋቋሙት ተቋማት መካከል የባዮ እና ኢመርንጂንግ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት አንዱ ነው፡፡

የኢንስቲትዩት ከፍተኛ ተመራማሪ ተስፋማሪያም በርሔ(ዶ/ር) እንደሚገልጹት የወተት ምርት አያያዝና አጠባበቅ አንዱ የትኩረት መስክ ነው።

በዚህም ኢንስቲትዩት ባደረገው ሳይንሳዊ ምርምር ባወጣው ስድስት አይነት የእርጎ እርሾዎች ወተትን በፍጥነት ማርጋትና ደህንነቱ ተጠብቆ እንዲቆይ ማድረግ መቻሉን ገልጸዋል።

ባክቴሪያዎች ወተትን እንዲረጋም፤ እንዲበላሽም መንስኤ እንደሆኑ ገልፀው፤ እርሾው ወተት በሰዓታት ውስጥ ረግቶ ግን ለቀናት ሳይበላሽ እንዲቆይ የሚያደርግ መሆኑን ተናግረዋል።

ከዚህ በፊት ወተት ለመርጋት እስከ አራት ቀን የሚወስደውን ጊዜ ከአራት እስከ ስድስት ሰዓት ማሳጠር መቻሉን ገልጸዋል።

የእርጎ እርሾ እርጎ ሳይበላሽ ከ10 ቀናት በላይ ማቀየት የሚያስችል መሆኑንም ገልጸው፤ ይህን የዜጎችን ጤና ከመጠበቅ ባለፈም ብክነት ለመከላከል የሚያግዝ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የምርምር ውጤቱ በግልና በኢንዱስትሪ ዕርጎ ለሚያመረቱ አምራቾች ከፍተኛ ጥቅም የሚሰጥ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ኩባንያዎች ከባዮ እና ኢመርንጂንግ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ጋር ውል በመግባት ምርቱን አምርተው ለገበያ ማቅረብ እንደሚችሉ ገልጿል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው &quot;ቡኖ - ማላ&quot; ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026