የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

<p>ኢንስቲትዩቱ እርጎን ከ10 ቀናት በላይ ሳይበላሽ ማቆየት የሚያስችል እርሾ አመረተ</p>

Feb 6, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ጥር 19/2017(ኢዜአ)፦ የባዮ እና ኢመርንጂንግ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ወተትን በሰዓታት ውስጥ ማርጋትና እርጎን ከ10 ቀናት በላይ ሳይበላሽ ማቆየት የሚያስችል እርሾ ማምረቱን ይፋ አደረገ፡፡

ከፍተኛ የቁም እንስሳት ሀብት ባላት ኢትዮጵያ ወተትን በነፍስ ወከፍ የመጠቀም ምጣኔ በዓመት ከ19 ሊትር አይበልጥም።

በዚህም መንግስት የወተት ኃብት ልማት ስትራቴጂ ነድፎ የሌማት ትሩፋትን ጨምሮ የወተት ምርታማነትንና የነፍስ ወከፍ ፍጆታን ለማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን በትኩረት እየሰራ ነው።

የወተት ልማቱን ማሳደግ፣ የወተት ምርት ላይ እሴቶችን መጨመር እና የምርት ጥራትና ደኅንነት ማስጠበቅ ላይ ትኩረት ተሰጥቷል።

በዘርፉ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማስፋት የተቀመጠውን ግብ ለማሳካት ከተቋቋሙት ተቋማት መካከል የባዮ እና ኢመርንጂንግ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት አንዱ ነው፡፡

የኢንስቲትዩት ከፍተኛ ተመራማሪ ተስፋማሪያም በርሔ(ዶ/ር) እንደሚገልጹት የወተት ምርት አያያዝና አጠባበቅ አንዱ የትኩረት መስክ ነው።

በዚህም ኢንስቲትዩት ባደረገው ሳይንሳዊ ምርምር ባወጣው ስድስት አይነት የእርጎ እርሾዎች ወተትን በፍጥነት ማርጋትና ደህንነቱ ተጠብቆ እንዲቆይ ማድረግ መቻሉን ገልጸዋል።

ባክቴሪያዎች ወተትን እንዲረጋም፤ እንዲበላሽም መንስኤ እንደሆኑ ገልፀው፤ እርሾው ወተት በሰዓታት ውስጥ ረግቶ ግን ለቀናት ሳይበላሽ እንዲቆይ የሚያደርግ መሆኑን ተናግረዋል።

ከዚህ በፊት ወተት ለመርጋት እስከ አራት ቀን የሚወስደውን ጊዜ ከአራት እስከ ስድስት ሰዓት ማሳጠር መቻሉን ገልጸዋል።

የእርጎ እርሾ እርጎ ሳይበላሽ ከ10 ቀናት በላይ ማቀየት የሚያስችል መሆኑንም ገልጸው፤ ይህን የዜጎችን ጤና ከመጠበቅ ባለፈም ብክነት ለመከላከል የሚያግዝ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የምርምር ውጤቱ በግልና በኢንዱስትሪ ዕርጎ ለሚያመረቱ አምራቾች ከፍተኛ ጥቅም የሚሰጥ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ኩባንያዎች ከባዮ እና ኢመርንጂንግ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ጋር ውል በመግባት ምርቱን አምርተው ለገበያ ማቅረብ እንደሚችሉ ገልጿል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026