የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

Jun 4, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ማግኘት መቻሉን የዞኑ እንስሳትና ዓሳ ሃብት መምሪያ አስታወቀ።

በመምሪያው የንብና ሃር ልማት ባለሙያ አቶ ስማቸው ዳምጤ ለኢዜአ እንደገለጹት በዞኑ የሚገኙ አርሶ አደሮችን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በንብ ማነብ ስራ በማሳተፍ ተጠቃሚ እንዲሆኑ እየተሰራ ነው።

በበጀት ዓመቱ በማነብ ስራ የተሰማሩ አርሶ አደሮችን በመደገፍና በማበረታታት ከ2 ነጥብ 1 ሚሊዮን ኪሎ ግራም በላይ ማር ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደ ስራ መገባቱን ገልጸዋል።

በዞኑ የሚገኙ ከ48 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች ባሏቸው ከ200 ሺህ በላይ የንብ ቀፎዎች እስካሁን ከ2 ነጥብ 9 ሚሊዮን ኪሎ ግራም በላይ ማር ማምረት መቻሉን ተናግረዋል።

የተመረተውን ማር ለገበያ በማቅረብ ከ1 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ማግኘት መቻሉን ገልጸዋል።


ምርቱም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ከ1 ሚሊዮን ኪሎ ግራም በላይ ብልጫ እንዳለው ጠቁመው ለዚህም የተስተካከለ ዝናብ መኖር ለዕፅዋት ማበብ ምክንያት በመሆኑ ምርቱ ሊጨምር መቻሉን አስረድተዋል።

ይህም ከአንድ ዘመናዊ ቀፎ በአማካኝ 30 ኪሎ ግራም፣ ከሽግግር ቀፎ 18 ኪሎ ግራምና ከባህላዊ ቀፎ ስምንት ኪሎ ግራም ማር እንዲገኝ በማስቻሉ የመጣ ውጤት መሆኑንም አብራርተዋል።

ከተሳታፊዎች መካከል የአዋበል ወረዳ የእነቢ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ጌታሁን ይግዛው፤ ከሰብል ልማቱ ጎን ለጎን በንብ ማነብ ስራ ላይ በመሰማራት ተጠቃሚ ሆኛለሁ ብለዋል።

በቅርብ ዓመታት በአረንጓዴ አሻራ የለሙ አካባቢዎች ለንብ ማነብ ስራ ምቹ ሁኔታ በመፍጠራቸው ከ10 ዘመናዊና የሽግግር ቀፎዎች ከ190 ኪሎ ግራም በላይ ምርት ማግኘታቸውንም ተናግረዋል።

የዚሁ ወረዳ የገሽ ቀበሌ ነዋሪ ወጣት ቢምረው አወቀ በበኩሉ ካሉት 13 ዘመናዊና የሽግግር የንብ ቀፎዎች ከ180 ሺህ ብር በላይ ገቢ ማግኘቱን ገልጿል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026