የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

Aug 13, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠቱን የክልሉ መሬት ቢሮ አስታወቀ።

በደሴ ከተማ አስተዳደር የገጠር ቀበሌ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር አሰጣጥ ሥነ ሥርዓት ዛሬ ተካሂዷል።


በሥነ- ሥርዓቱ ላይ የአማራ ክልል መሬት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሲሳይ ዳምጤ እንደገለጹት፤ የክልሉን መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም በማዘመን የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ማሳደግ ተችሏል።

በክልሉ ባለፉት ዓመታት የአርሶ አደሮችን ዘላቂ የመሬት ባለቤትነትና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተደረገው ጥረት ተጨባጭ ውጤት እንዳስገኘ ተናግረዋል።

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ብቻ ከ488 ሺህ በላይ የመሬት ይዞታዎች ላይ የሁለተኛ ደረጃ ማረጋገጫ ደብተር መስጠት መቻሉን ገልጸዋል።

የይዞታ ደብተሩ የአርሶ አደሩን ይዞታ በዘመናዊ መንገድ በመለካትና ማረጋገጫ በመስጠት የብድርና ሌሎች አገልግሎቶችን ተጠቃሚ ለማድረግ ሰፊ ዕድል የፈጠረ መሆኑንም አመልክተዋል።

እንዲሁም ቀደም ሲል በመሬት ወሰንና ድንበር አካባቢ የሚፈጠሩ ግጭቶችን፣ አለመግባባቶችንና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ከማስቀረቱ ባለፈ ትክክለኛ ግብር መክፈል እንዲቻል የሚያደርግ መሆኑን አስረድተዋል።

በበጀት ዓመቱ ከ43 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተራቸውን ዋስትና በማስያዝ ከ3 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር በላይ ብድር መውሰዳቸውን ገልጸዋል።


በዛሬው ዕለትም በደሴ ከተማ አስተዳደር ለ996 አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መስጠት መቻሉን ገልጸው፣ በአዲሱ በጀት ዓመትም ሥራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።

የደሴ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ሳሙኤል ሞላልኝ በበኩላቸው፤ በከተማው የገጠር መሬት አያያዝና አጠቃቀምን በማዘመን የአርሶ አደሩን የመሬት ባለቤትነትና ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል።

መሬቱን በሳይንሳዊ መንገድ በመለካት ትክክለኛ መገኛውን፣ ድንበሩን፣ ወሰኑንና መጠኑን በማስቀመጥ ለአርሶ አደሩ የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር እየተሰጠ መሆኑን አመልክተዋል።


ይህም ሕገ-ወጥ መሬት ወረራንና ግንባታን በማስቀረት የመልካም አስተዳደር ችግሮችን እያቃለለ መሆኑን አስገንዝበዋል።

በደሴ ከተማ የዋሊዶ ገጠር ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር አሊ ሁሴን እና ወይዘሮ ደመቁ ሁሴን፤ የይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ማግኘታችን መሬቱን በተሻለ መንገድ ለማልማትና ተጨማሪ ሀብት ለማፍራት ያስችለናል ነው ያሉት።

የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተሩ ወሰንና ልኬትን በትክክል ያስቀመጠ በመሆኑ የመሬታችንን ዘላቂ ዋስትና እና ተጠቃሚነት ያረጋገጠ ነው ብለዋል።

በሥነ ሥርዓቱ ላይ የክልልና የከተማ አመራሮችን ጨምሮ ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026

የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሙ ግልጽነትና ተጠያቂነት የሰፈነበት የመንግሥት ኤሌክትሮኒክ ግዥ ስርዓት ውጤታማነትን አሻሽሏል

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦ የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሙ ግልጽነትና ተጠያቂነት የሰፈነበት የመንግሥት ኤሌክትሮኒክ ግዥ ስርዓትንና የወጪ ውጤታማነትን ማ...

Jul 31, 2026

በአስተዳደሩ በበጀት ዓመቱ ከ7 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ በመሰብሰብ የነዋሪውን የልማት ጥያቄ ለመመለስ ጥረት ተደርጓል

ድሬደዋ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦ በበጀት ዓመቱ ከ7 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ በመሰብሰብ የነዋሪውን የልማት ጥያቄ ለመመለስ ጥረት መደረጉን የድሬደዋ አስተዳ...

Jul 20, 2026