🔇Unmute
ባህር ዳር፤ መስከረም 4/2019 (ኢዜአ)፦ በደቡብ ጎንደር ዞን በመኸር ወቅት ከለማው 641 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ ከ28 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ የሚያስችል የተባይ አሰሳና የአረም መከላከል ስራ እየተከናወነ ይገኛል።

የዞኑ ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ የሺጥላ ፈቃዴ እንደገለጹት፤ በዞኑ በኩታ ገጠም አሰራር እየለሙ ያሉትን እንደ ሩዝ፣ ጤፍ፣ ስንዴ እና ገብስ ያሉ ሰብሎችን ከአረምና ተባይ ነፃ ለማድረግ ጥረት እየተደረገ ነው። ሙሉ የግብርና ፓኬጅ፣ የተሻሻሉ ቴክኖሎጂዎችና የአፈር ለምነት ማሻሻያዎች በጥቅም ላይ በመዋላቸው ሰብሉ በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝና የታቀደው ምርት እንደሚገኝ ተናግረዋል።

የዞኑ አርሶ አደሮች በበኩላቸው፤ በባለሙያዎች ምክረ-ሃሳብ ታግዘው ማሳቸውን በየዕለቱ በመቃኘትና በማረም ላይ እንደሚገኙ ገልጸው፣ የኩታ ገጠም አሰራርና ዘመናዊ ግብዓቶችን መጠቀም ከቤተሰብ ፍጆታ የተረፈ ምርት ለገበያ ለማቅረብ እንዳስቻላቸው ገልጸዋል።

ባህር ዳር፤ መስከረም 4/2019 (ኢዜአ)፦ በደቡብ ጎንደር ዞን በመኸር ወቅት ከለማው 641 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ ከ28 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰ...
Sep 15, 2026
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026