🔇Unmute
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት ፍቃድ ስረዛና እገዳ እርምጃ መወሰዱን የክልሉ ኢንተርፕራይዝ ልማትና ኢንዱስትሪ ቢሮ አስታወቀ።
የክልሉ ኢንተርፕራይዝ ልማትና ኢንዱስትሪ ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ሀምዲ ሰለሃዲን ለኢዜአ እንዳሉት የክልሉ መንግሥት በኢንቨስትመንት ተሰማርተው ለሚገኙና አዳዲስ ለሚሰማሩ ባለሀብቶች ምቹ ሁኔታን እየፈጠረ ይገኛል።
ከዚህም ባለፈ የባለሀብቶች እንቅስቃሴ ያለበትን ሁኔታ የመስክ ምልከታ በማከናወን በገቡት ውል መሰረት ወደ ስራ ያልገቡ ባለሃብቶች ላይ እርምጃ እየወሰደ እንደሚገኝም ገልጸዋል።

ባለሀብቱ ከመንግስት የኢንቨስትመንት ፈቃድና መሬት የሚወስደው የክልሉን ልማት ለማፋጠን በመሆኑ የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባም ነው ያሳሰቡት።
በዚህም በክልሉ በኢንቨስትመንት አዋጅ፣ ደንብና መመሪያ መሠረት ቀደም ሲል የኢንቨስትመንት ፈቃድና መሬት ወስደው ወደስራ ያልገቡና ግንባታ ያጓተቱ 3 ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መሰረዙን ተናግረዋል።
እንዲሁም መሬት ወስደው በውሉ መሠረት ወደ ግንባታ ሥራ ባልገቡና የሼድ ግንባታ አጠናቀው ወደ ማምረት ባልገቡ 9 ባለሀብቶች ላይ ደግሞ ፈቃድ የማገድ እርምጃ መውሰዱን አስታውቀዋል።
ከዚህ በተጨማሪም የኢንቨስትመንት ፈቃድና መሬት ወስደው አዝጋሚ የግንባታ ሂደት ውስጥ ለሚገኙ 7 ባለሀብቶችም የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷል ብለዋል።
በባለሀብቶቹ ላይ ከሚወሰደው እርምጃ ጎን ለጎንም ባለሀብቶቹ የሚያጋጥሟቸውን ችግሮች የመፍታት ሥራ ተከናውኗል ሲሉ ተናግረዋል።
በባለሀብቶቹ ላይ እርምጃ መወሰድ መጀመሩም የሌሎች ፕሮጀክቶች ግንባታ ሥራዎች እንዲፋጠኑ ዕድል መፍጠሩን ጠቁመው በቀጣይም መሰል እርምጃዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አመልክተዋል።

በቀጣይም ባለሀብቶቹ ወደ ሥራ ካልገቡ ፈቃድ በመሰረዝ የወሰዱት መሬት ለመሬት ባንክ ገቢ እንደሚደረግ አስታውቀዋል።
በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በክልሉ ከ3 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ 96 ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መሰጠቱን ጠቅሰዋል።
ለባለሀብቶቹም የኢንቨስትመንት ፈቃድ የተሰጣቸው በማኑፋክቸሪንግ፣ ሆቴል፣ ግብርና፣ በገበያ ማዕከልና በሌሎች ዘርፎች ለመሰማራት ጥያቄ በማቅረባቸው መሆኑን ተናግረዋል።
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦ የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሙ ግልጽነትና ተጠያቂነት የሰፈነበት የመንግሥት ኤሌክትሮኒክ ግዥ ስርዓትንና የወጪ ውጤታማነትን ማ...
Jul 31, 2026