የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

Aug 27, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ ገለጹ፡፡

ሀዋሳ ከተማን ሳቢ፣ ምቹና ይበልጥ ተመራጭ ለማድረግ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎች በርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ እና በሌሎች የሥራ ሃላፊዎች ተጎብኝቷል።


ርዕሰ መስተዳድሩ በዚህ ወቅት እንዳሉት ከተማዋ ያላት የተፈጥሮ ውበት ይበልጥ ጎልቶ እንዲወጣ የኮሪደር ልማት ሥራው ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል።

በአሁኑ ወቅት ግንባታው እየተካሄደ ያለው የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎች ከተማዋን ይበልጥ ለኑሮ፣ ለኢንቨስትመንት፣ ለመዝናኛነት እና ለኮንፈረንስ ምቹና ተመራጭ እንደሚያደርጋት ጠቁመዋል።


እነዚህ የልማት ሥራዎች በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ ተጠናቀው ለአገልግሎት እንዲበቁ የክልሉ መንግስት መላውን ህዝብ በማስተባበር አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል።


የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነ በበኩላቸው በከተማዋ ለአራተኛ ዙር እየከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት ሥራ ከጥቃቅን ሥራዎች በስተቀር ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ መጠናቀቁን አስታውቀዋል።

የሀዋሳ ሐይቅ ዳርቻ ልማት ሥራም በተያዘለት ጊዜ ለማጠናቀቅ በቀን ለ24 ሰዓታት እየተሰራ መሆኑን አመልክተዋል።

ለሐይቅ ዳርቻ ልማቱ ህዝቡን በማስተባበር እስካሁን ድረስ 1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ መቻሉንም ተናግረዋል።

በልማት ሥራዎች ጉብኝት ላይ የሲዳማ ክልልና የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026