
አዲስ አበባ፤ ጥር 28/2017(ኢዜአ)፡- አዲስ አበባ ከተማን ከሸገር ከተማ የሚያገናኙ አዳዲስ እና ነባር መንገዶች ግንባታ እና ማስፋፊያ እየተከናወነ መሆኑን የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር አስታወቀ።
የመንገዶቹን ግንባታ ከተለያዩ የመገናኛ ብዙሃን ተቋማት የተውጣጡ ባለሙያዎች እየጎበኙ ይገኛሉ።
የሸገር ከተማን የሚያቋርጡ እና በሁሉም አቅጣጫ ወደ አዲስ አበባ የሚያስገቡ መንገዶች ከፍተኛ የትራፊክ ፍሰት ያለባቸው በመሆኑ መንገዶቹን ለማሻሻል የጥናት ስራዎች መከናወናቸው ተገልጿል፡፡
በዚህም በአጭር፣ በመካከለኛና በረጅም ጊዜ ችግሮችን በመፍታት የትራፊክ ፍሰቱን ለማስተካከል ደረጃቸውን የጠበቁ መንገዶች ግንባታ በመካሄድ ላይ ነው ተብሏል።

የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች በግንባታ ላይ የሚገኙ አዲስ አበባ - ሆለታ መንገድ ማሻሻያ ፕሮጀከት፣ ከእንጦጦ ማርያም ጉለሌ ዕፅዋት ማዕከል እና ከስፔስ ኦብዘርቫቶሪ ጫካ መንደር ፕሮጀክት መንገዶች ግንባታን ጎብኝተዋል፡፡
የመንገዶቹ ግንባታ ደረጃቸውን ጠብቀው እንዲጠናቀቁ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ክትትልና ድጋፍ እያደረገ መሆኑንም ገልጿል።
አዲስ አበባን ከሸገር ከተማ ከሚያገናኙ መንገዶች መካከል የጣፎ አደባባይ - ለገዳዲ - ኩራ - ጂዳ መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት አንዱ መሆኑንና ግንባታው በቅርቡ እንደሚጀመርም ተጠቁሟል።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026