የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

<p>አዲስ አበባ ከተማን ከሸገር ከተማ የሚያገናኙ አዳዲስ እና ነባር መንገዶች ግንባታ እና ማስፋፊያ እየተከናወነ ነው</p>

Feb 6, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ጥር 28/2017(ኢዜአ)፡- አዲስ አበባ ከተማን ከሸገር ከተማ የሚያገናኙ አዳዲስ እና ነባር መንገዶች ግንባታ እና ማስፋፊያ እየተከናወነ መሆኑን የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር አስታወቀ።

የመንገዶቹን ግንባታ ከተለያዩ የመገናኛ ብዙሃን ተቋማት የተውጣጡ ባለሙያዎች እየጎበኙ ይገኛሉ።

የሸገር ከተማን የሚያቋርጡ እና በሁሉም አቅጣጫ ወደ አዲስ አበባ የሚያስገቡ መንገዶች ከፍተኛ የትራፊክ ፍሰት ያለባቸው በመሆኑ መንገዶቹን ለማሻሻል የጥናት ስራዎች መከናወናቸው ተገልጿል፡፡

በዚህም በአጭር፣ በመካከለኛና በረጅም ጊዜ ችግሮችን በመፍታት የትራፊክ ፍሰቱን ለማስተካከል ደረጃቸውን የጠበቁ መንገዶች ግንባታ በመካሄድ ላይ ነው ተብሏል።


የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች በግንባታ ላይ የሚገኙ አዲስ አበባ - ሆለታ መንገድ ማሻሻያ ፕሮጀከት፣ ከእንጦጦ ማርያም ጉለሌ ዕፅዋት ማዕከል እና ከስፔስ ኦብዘርቫቶሪ ጫካ መንደር ፕሮጀክት መንገዶች ግንባታን ጎብኝተዋል፡፡

የመንገዶቹ ግንባታ ደረጃቸውን ጠብቀው እንዲጠናቀቁ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ክትትልና ድጋፍ እያደረገ መሆኑንም ገልጿል።

አዲስ አበባን ከሸገር ከተማ ከሚያገናኙ መንገዶች መካከል የጣፎ አደባባይ - ለገዳዲ - ኩራ - ጂዳ መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት አንዱ መሆኑንና ግንባታው በቅርቡ እንደሚጀመርም ተጠቁሟል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው &quot;ቡኖ - ማላ&quot; ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026