የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

<p>አዲስ አበባ ከተማን ከሸገር ከተማ የሚያገናኙ አዳዲስ እና ነባር መንገዶች ግንባታ እና ማስፋፊያ እየተከናወነ ነው</p>

Feb 6, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ጥር 28/2017(ኢዜአ)፡- አዲስ አበባ ከተማን ከሸገር ከተማ የሚያገናኙ አዳዲስ እና ነባር መንገዶች ግንባታ እና ማስፋፊያ እየተከናወነ መሆኑን የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር አስታወቀ።

የመንገዶቹን ግንባታ ከተለያዩ የመገናኛ ብዙሃን ተቋማት የተውጣጡ ባለሙያዎች እየጎበኙ ይገኛሉ።

የሸገር ከተማን የሚያቋርጡ እና በሁሉም አቅጣጫ ወደ አዲስ አበባ የሚያስገቡ መንገዶች ከፍተኛ የትራፊክ ፍሰት ያለባቸው በመሆኑ መንገዶቹን ለማሻሻል የጥናት ስራዎች መከናወናቸው ተገልጿል፡፡

በዚህም በአጭር፣ በመካከለኛና በረጅም ጊዜ ችግሮችን በመፍታት የትራፊክ ፍሰቱን ለማስተካከል ደረጃቸውን የጠበቁ መንገዶች ግንባታ በመካሄድ ላይ ነው ተብሏል።


የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች በግንባታ ላይ የሚገኙ አዲስ አበባ - ሆለታ መንገድ ማሻሻያ ፕሮጀከት፣ ከእንጦጦ ማርያም ጉለሌ ዕፅዋት ማዕከል እና ከስፔስ ኦብዘርቫቶሪ ጫካ መንደር ፕሮጀክት መንገዶች ግንባታን ጎብኝተዋል፡፡

የመንገዶቹ ግንባታ ደረጃቸውን ጠብቀው እንዲጠናቀቁ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ክትትልና ድጋፍ እያደረገ መሆኑንም ገልጿል።

አዲስ አበባን ከሸገር ከተማ ከሚያገናኙ መንገዶች መካከል የጣፎ አደባባይ - ለገዳዲ - ኩራ - ጂዳ መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት አንዱ መሆኑንና ግንባታው በቅርቡ እንደሚጀመርም ተጠቁሟል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025