የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

<p>በአሶሳ ከተማ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎች የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ናቸው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል</p>

Feb 24, 2025

IDOPRESS

አሶሳ፤ የካቲት 15/2017 (ኢዜአ):- በአሶሳ ከተማ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎች የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ መሆናቸውን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር እና የብልጽግና ፓርቲ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል ሙፈሪሃት ካሚል ተናገሩ።

ሚኒስትሯ የአሶሳ ከተማን የአስፓልት መንገድ እና የኮሪደር ልማት ስራ ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።

ከጉብኝታቸው በኋላ ሚኒስትሯ ለሚዲያ አካላት እንደገለፁት በከተማዋ እየተከናወኑ ያሉ የመሠረተ ልማት ግንባታዎች ሰው ተኮር እና የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ናቸው።


በከተማዋ እየተከናወኑ የሚገኙት የአስፓልት መንገድ፣ የኮሪደር ልማት ስራ እንዲሁም የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ግንባታ በፍጥነት እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል።

የልማት ስራዎቹ ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል ከመፍጠራቸው በተጨማሪ ዜጎች የመሥራት ክህሎታቸውን እንዲያዳብሩ ያደርጋል ብለዋል።

የዜጎችን ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማረጋገጥ የሚከናወኑ የመሠረተ ልማት ስራዎች የዜጎችን ህይወት የሚቀይሩና አካታች መሆናቸውን ገልጸዋል።

የአካባቢው ማህበረሰብ የሚያገኘውን ሀብት በመጠቀም በከተማዋ የጀመረው የኢንቨስትመንት ስራ የሚበረታታ ነው ብለዋል።


ከህዳሴ ግድብ ጋር ተያይዞ የከተማዋን የወደፊት ዕድገት ታሳቢ ያደረገ የገበያ ማዕከል እና የመሠረተ ልማት ግንባታዎችን መመልከታቸውን ጠቁመዋል።

በተጨማሪም ሚኒስትሯ በመደመር መጽሃፍ ገቢ እየተገነባ ያለውን ሙዚየም ጎብኝተዋል።

በጉብኝቱ በብልጽግና ፓርቲ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ኢሳቅ አብዱልቃድር እና የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026