
አሶሳ፤ የካቲት 15/2017 (ኢዜአ):- በአሶሳ ከተማ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎች የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ መሆናቸውን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር እና የብልጽግና ፓርቲ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል ሙፈሪሃት ካሚል ተናገሩ።
ሚኒስትሯ የአሶሳ ከተማን የአስፓልት መንገድ እና የኮሪደር ልማት ስራ ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።
ከጉብኝታቸው በኋላ ሚኒስትሯ ለሚዲያ አካላት እንደገለፁት በከተማዋ እየተከናወኑ ያሉ የመሠረተ ልማት ግንባታዎች ሰው ተኮር እና የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ናቸው።

በከተማዋ እየተከናወኑ የሚገኙት የአስፓልት መንገድ፣ የኮሪደር ልማት ስራ እንዲሁም የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ግንባታ በፍጥነት እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል።
የልማት ስራዎቹ ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል ከመፍጠራቸው በተጨማሪ ዜጎች የመሥራት ክህሎታቸውን እንዲያዳብሩ ያደርጋል ብለዋል።
የዜጎችን ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማረጋገጥ የሚከናወኑ የመሠረተ ልማት ስራዎች የዜጎችን ህይወት የሚቀይሩና አካታች መሆናቸውን ገልጸዋል።
የአካባቢው ማህበረሰብ የሚያገኘውን ሀብት በመጠቀም በከተማዋ የጀመረው የኢንቨስትመንት ስራ የሚበረታታ ነው ብለዋል።

ከህዳሴ ግድብ ጋር ተያይዞ የከተማዋን የወደፊት ዕድገት ታሳቢ ያደረገ የገበያ ማዕከል እና የመሠረተ ልማት ግንባታዎችን መመልከታቸውን ጠቁመዋል።
በተጨማሪም ሚኒስትሯ በመደመር መጽሃፍ ገቢ እየተገነባ ያለውን ሙዚየም ጎብኝተዋል።
በጉብኝቱ በብልጽግና ፓርቲ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ኢሳቅ አብዱልቃድር እና የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026