
አዲስ አበባ፤ የካቲት 18/2017(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ባለፉት ሁለት ዓመታት 50 ሺህ ኪሎ ሜትር መንገድ ጥገና መከናወኑን የክልሉ መንገድና ሎጂስቲክስ ቢሮ አስታወቀ።
ቢሮው በክልሉ የመንገድ ተደራሽነትን የሚያሰፉና ህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚሳድጉ የመንገድ ልማትና ጥገና ስራ ሲያከናወን መቆየቱን ገልጿል።
በኦሮሚያ ኮሙኒኬሽን ቢሮ በሚዘጋጀው 'ጉሚ በልበሎሚ' የውይይት መድረክ በመንገድ ጥገና እና የፕሮጀክቶች መጓተትና ጥራት ችግሮች እንዳሉ ተነስቷል።
የቢሮ ሃላፊ ጫላ አብዲ(ኢንጂነር) በመድረኩ ላይ እንዳሉት በዘርፉ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት በሁሉም የክልሉ ዞኖች የመንገድ ግንባታና ጥገና ሥራዎች እየተከናወነ ነው።
በክልሉ ቀበሌን ከቀበሌ፣ ወረዳን ከወረዳ እንዲሁም ከዋና ዋና መንገዶች ጋር የሚያገናኙ የመንገድ ግንባታና ጥገና መከናወኑን አንስተዋል።
ባለፉት ሁለት ዓመታት የመንገድ ፈንድ በማቋቋም 50 ሺህ ኪሎ ሜትር መንገድ የመጠገኑን ለአብነት ጠቅሰዋል።
በተያዘው በጀት ዓመትም የመንገድ ተደራሽነትን ለማስፋት አዲስ የመንገድ ዝርጋታና ጥገና ላይ ሰፊ ስራዎችን እየተሰራ ነው ብለዋል።
በሌላ በኩል በፌደራልና በክልሉ መንግስት መንገድ ፈንድ በኩል 7 ሺህ 44 ኪሎ ሜትር መንገድ ከባድና ቀላል ጥገና ለማከናወን በ1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር በጀት መያዙን አስታውቀዋል።
ቢሮው የጥገና አቅሙን ለማጎልበት ባለፉት ዓመታት ግዙፍ የጥገና ማሽኖችን መግዛቱን አስታውሰዋል።
"ጉሚ በልበሎሚ" የኦሮሚያ ክልል ኮሙኒኬሽን ቢሮ የህዝብ ጥያቄ በመሰብሰብና ሰፊ ጥናት በማካሄድ ጉዳዩ ከሚመለከታቸው ሴክተር መሥሪያ ቤቶች ምላሽ የሚጠይቅበት የውይይት መድረክ ነው።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026