
አዲስ አበባ፤ የካቲት 18/2017(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ባለፉት ሁለት ዓመታት 50 ሺህ ኪሎ ሜትር መንገድ ጥገና መከናወኑን የክልሉ መንገድና ሎጂስቲክስ ቢሮ አስታወቀ።
ቢሮው በክልሉ የመንገድ ተደራሽነትን የሚያሰፉና ህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚሳድጉ የመንገድ ልማትና ጥገና ስራ ሲያከናወን መቆየቱን ገልጿል።
በኦሮሚያ ኮሙኒኬሽን ቢሮ በሚዘጋጀው 'ጉሚ በልበሎሚ' የውይይት መድረክ በመንገድ ጥገና እና የፕሮጀክቶች መጓተትና ጥራት ችግሮች እንዳሉ ተነስቷል።
የቢሮ ሃላፊ ጫላ አብዲ(ኢንጂነር) በመድረኩ ላይ እንዳሉት በዘርፉ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት በሁሉም የክልሉ ዞኖች የመንገድ ግንባታና ጥገና ሥራዎች እየተከናወነ ነው።
በክልሉ ቀበሌን ከቀበሌ፣ ወረዳን ከወረዳ እንዲሁም ከዋና ዋና መንገዶች ጋር የሚያገናኙ የመንገድ ግንባታና ጥገና መከናወኑን አንስተዋል።
ባለፉት ሁለት ዓመታት የመንገድ ፈንድ በማቋቋም 50 ሺህ ኪሎ ሜትር መንገድ የመጠገኑን ለአብነት ጠቅሰዋል።
በተያዘው በጀት ዓመትም የመንገድ ተደራሽነትን ለማስፋት አዲስ የመንገድ ዝርጋታና ጥገና ላይ ሰፊ ስራዎችን እየተሰራ ነው ብለዋል።
በሌላ በኩል በፌደራልና በክልሉ መንግስት መንገድ ፈንድ በኩል 7 ሺህ 44 ኪሎ ሜትር መንገድ ከባድና ቀላል ጥገና ለማከናወን በ1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር በጀት መያዙን አስታውቀዋል።
ቢሮው የጥገና አቅሙን ለማጎልበት ባለፉት ዓመታት ግዙፍ የጥገና ማሽኖችን መግዛቱን አስታውሰዋል።
"ጉሚ በልበሎሚ" የኦሮሚያ ክልል ኮሙኒኬሽን ቢሮ የህዝብ ጥያቄ በመሰብሰብና ሰፊ ጥናት በማካሄድ ጉዳዩ ከሚመለከታቸው ሴክተር መሥሪያ ቤቶች ምላሽ የሚጠይቅበት የውይይት መድረክ ነው።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026