አዲስ አበባ ፤የካቲት 18/2017 ( ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ጃንግዙ የኢኮኖሚና የንግድ ትብብር ኮንፈረንስ የቻይና ባለሀብቶች በኢትዮጵያ ያለውን ምቹ የኢንቨስትመንት እድል በጥልቀት እንዲመለከቱ እንደሚያግዝ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን አስታወቀ።
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ምክትል ኮምሽነር ዝናብ ይርጋ ኮንፍረንሱ የኢትዮጵያና የቻይና ረጅም ዘመናት ያስቆጠረ የንግድ፣የኢኮኖሚና የኢንቨስትመንት ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሻግር ጠቁመዋል።
ምክትል ኮምሽነሩ አክለውም ይህን መሰል ዝግጅት የቻይና ባለሀብቶች በኢትዮጵያ ያለውን ምቹ የኢንቨስትመንት እድል በጥልቀት እንዲመለከቱ ያግዛል ብለዋል።
በማኑፋክቸሪንግና በአይ ሲ ቲ ግዙፍ ስም ያላቸው የጆንግዙ የንግድ ልኡካን በኢትዮጵያ መዋዕለንዋያቸውን ቢያፈሱ ኮምሽኑ አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን ተናግረዋል ።
በወቅቱ በሀገሪቱ ስላሉ የኢንቨስትመንት እድሎች ማብራሪያ የተሰጠ ሲሆን በኮንፈረንሱ ከ200 በላይ የጃንግዙና የኢትዮጵያ የንግዱ ማህበረሰብ መሳተፋቸውን ከኮሚሽኑ የተገኘ መረጃ ያመለክታል።
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...
Feb 12, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...
Feb 8, 2025