
አዲስ አበባ ፤የካቲት 18/2017 ( ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ጃንግዙ የኢኮኖሚና የንግድ ትብብር ኮንፈረንስ የቻይና ባለሀብቶች በኢትዮጵያ ያለውን ምቹ የኢንቨስትመንት እድል በጥልቀት እንዲመለከቱ እንደሚያግዝ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን አስታወቀ።
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ምክትል ኮምሽነር ዝናብ ይርጋ ኮንፍረንሱ የኢትዮጵያና የቻይና ረጅም ዘመናት ያስቆጠረ የንግድ፣የኢኮኖሚና የኢንቨስትመንት ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሻግር ጠቁመዋል።
ምክትል ኮምሽነሩ አክለውም ይህን መሰል ዝግጅት የቻይና ባለሀብቶች በኢትዮጵያ ያለውን ምቹ የኢንቨስትመንት እድል በጥልቀት እንዲመለከቱ ያግዛል ብለዋል።
በማኑፋክቸሪንግና በአይ ሲ ቲ ግዙፍ ስም ያላቸው የጆንግዙ የንግድ ልኡካን በኢትዮጵያ መዋዕለንዋያቸውን ቢያፈሱ ኮምሽኑ አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን ተናግረዋል ።
በወቅቱ በሀገሪቱ ስላሉ የኢንቨስትመንት እድሎች ማብራሪያ የተሰጠ ሲሆን በኮንፈረንሱ ከ200 በላይ የጃንግዙና የኢትዮጵያ የንግዱ ማህበረሰብ መሳተፋቸውን ከኮሚሽኑ የተገኘ መረጃ ያመለክታል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026