
አዲስ አበባ ፤የካቲት 18/2017 ( ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ጃንግዙ የኢኮኖሚና የንግድ ትብብር ኮንፈረንስ የቻይና ባለሀብቶች በኢትዮጵያ ያለውን ምቹ የኢንቨስትመንት እድል በጥልቀት እንዲመለከቱ እንደሚያግዝ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን አስታወቀ።
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ምክትል ኮምሽነር ዝናብ ይርጋ ኮንፍረንሱ የኢትዮጵያና የቻይና ረጅም ዘመናት ያስቆጠረ የንግድ፣የኢኮኖሚና የኢንቨስትመንት ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሻግር ጠቁመዋል።
ምክትል ኮምሽነሩ አክለውም ይህን መሰል ዝግጅት የቻይና ባለሀብቶች በኢትዮጵያ ያለውን ምቹ የኢንቨስትመንት እድል በጥልቀት እንዲመለከቱ ያግዛል ብለዋል።
በማኑፋክቸሪንግና በአይ ሲ ቲ ግዙፍ ስም ያላቸው የጆንግዙ የንግድ ልኡካን በኢትዮጵያ መዋዕለንዋያቸውን ቢያፈሱ ኮምሽኑ አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን ተናግረዋል ።
በወቅቱ በሀገሪቱ ስላሉ የኢንቨስትመንት እድሎች ማብራሪያ የተሰጠ ሲሆን በኮንፈረንሱ ከ200 በላይ የጃንግዙና የኢትዮጵያ የንግዱ ማህበረሰብ መሳተፋቸውን ከኮሚሽኑ የተገኘ መረጃ ያመለክታል።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026