
አሶሳ፤ መጋቢት 8/2017(ኢዜአ):- በህዝብ ተወካዮች ምክርቤት የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ተመራጮች ከክልሉ ከፍተኛ አመራር አባላት ጋር ተወያዩ።
ውይይቱ የተደረገው የህዝብ ተወካዮቹ በክልሉ ከመራጮች ጋር ምክክር ሲያደርጉ ቆይተው የተነሱ ጥያቄዎችን መሠረት በማድረግ ነው።
በውይይቱ ላይ ሪፖርት ያቀረቡት የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት አባል አቶ ሙባረክ ኤሊያስ፤ ከህብረተሰቡ ጋር በተደረገው ውይይት የልማት እና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች መነሳታቸውን ጠቅሰዋል።

ለአብነትም የፌዴራል መንግስትን እገዛ የሚጠይቁ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት እጥረት፣ የኔትወርክ ማሻሻያ፣ የመንገድ እና ሌሎች የመሠረተ ልማት ጥያቄዎች ተነስተዋል ብለዋል።
የክልሉ መንግስት የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ማሻሻል፣ የጤና ተቋማት ግንባታ እና የተጀመሩ የልማት ፕሮጀክቶች በፍጥነት እንዲጠናቀቁ ተጠይቋል።
በውይይት መድረኩ ላይ የተገኙት የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻደሊ ሐሰን በበኩላቸው፤ በህብረተሰቡ የተነሱት የልማት ጥያቄዎችን ደረጃ በደረጃ ለመመለስ እየተሰራ ነው ብለዋል።

በተለይ የመንገድ እና የትራንስፖርት አገልግሎትን ለማስፋፋት ከፌዴራል መንግስት ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
በክልሉ የተገኘውን ሰላም ለማፅናት ህብረተሰቡን ያሳተፈ የውይይት መድረክ እየተካሄደ መሆኑን ርዕሰ መስተዳድሩ ጠቁመዋል።
በመድረኩ ላይ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ -ጉባዔ አስካለች አልቦሮን ጨምሮ ሌሎችም ከፍተኛ አመራር አባላት ተገኝተዋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026