የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ተመራጮቹ ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከፍተኛ አመራር አባላት ጋር ተወያዩ

Mar 18, 2025

IDOPRESS

አሶሳ፤ መጋቢት 8/2017(ኢዜአ):- በህዝብ ተወካዮች ምክርቤት የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ተመራጮች ከክልሉ ከፍተኛ አመራር አባላት ጋር ተወያዩ።

ውይይቱ የተደረገው የህዝብ ተወካዮቹ በክልሉ ከመራጮች ጋር ምክክር ሲያደርጉ ቆይተው የተነሱ ጥያቄዎችን መሠረት በማድረግ ነው።

በውይይቱ ላይ ሪፖርት ያቀረቡት የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት አባል አቶ ሙባረክ ኤሊያስ፤ ከህብረተሰቡ ጋር በተደረገው ውይይት የልማት እና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች መነሳታቸውን ጠቅሰዋል።


ለአብነትም የፌዴራል መንግስትን እገዛ የሚጠይቁ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት እጥረት፣ የኔትወርክ ማሻሻያ፣ የመንገድ እና ሌሎች የመሠረተ ልማት ጥያቄዎች ተነስተዋል ብለዋል።

የክልሉ መንግስት የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ማሻሻል፣ የጤና ተቋማት ግንባታ እና የተጀመሩ የልማት ፕሮጀክቶች በፍጥነት እንዲጠናቀቁ ተጠይቋል።

በውይይት መድረኩ ላይ የተገኙት የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻደሊ ሐሰን በበኩላቸው፤ በህብረተሰቡ የተነሱት የልማት ጥያቄዎችን ደረጃ በደረጃ ለመመለስ እየተሰራ ነው ብለዋል።


በተለይ የመንገድ እና የትራንስፖርት አገልግሎትን ለማስፋፋት ከፌዴራል መንግስት ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

በክልሉ የተገኘውን ሰላም ለማፅናት ህብረተሰቡን ያሳተፈ የውይይት መድረክ እየተካሄደ መሆኑን ርዕሰ መስተዳድሩ ጠቁመዋል።

በመድረኩ ላይ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ -ጉባዔ አስካለች አልቦሮን ጨምሮ ሌሎችም ከፍተኛ አመራር አባላት ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026