የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ኢትዮጵያ በግብርና ልማት ለሌሎች ሀገራት ተምሳሌት የሚሆኑ ሥራዎችን እያከናወነች ነው

Apr 22, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 13/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጰያ በግብርና ልማት ለሌሎች ሀገራት ተምሳሌት የሚሆኑ ሥራዎችን እያከናወነች መሆኑ ተገልጿል።

የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎችን አፈጻጸም በተመለከተ ባለድርሻ አካላት ግምገማ አድርገዋል።

የምስራቅ አፍሪካ የልማት በየነ መንግስታት ባለስልጣን(ኢጋድ) አባል ሀገራት የግብርና ልማት አፈጻጸምን በተመለከተ የአፍሪካ የግብርና ልማት ፕሮግራም በየሁለት ዓመቱ ይገመግማል።

ሀገራቱ ለፕሮግራሙ ሪፖርት ከማድረጋቸው በፊት ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ የውይይት መድረክ በማዘጋጀት የየሀገራቸውን አፈጻጸም ይገመግማሉ።

በዚህ መሰረት ኢትዮጵያም የግብርና ልማት ስራዎቿን አፈጻጸም ገምግማለች።

በግብርና ሚኒስቴር የሚኒስትሩ አማካሪ አቶ ዜና ሃብተወልድ እንደሚሉት፣ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የግብርና ልማት ፕሮግራም የተሻለ አፈፃፀም አላት።

ፕሮግራሙ ያስቀመጣቸው መስፈርቶችን በልማት ዕቅዷ በማካተት ተግባራዊ ማድረጓ ለውጤቱ መገኘት ትልቅ ድርሻ ማበርከቱን ጠቅሰዋል።

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት፣ በአረንጓዴ አሻራ፣ በሌማት ትሩፋትና በሌሎች የግብርና ልማት ስራዎች እያስመዘገበችው ያለው ስኬት ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ምሳሌ የሚሆን ነው ብለዋል።

በኢጋድ የምግብ ሥርዓት ፕሮግራም አስተባባሪ ሰናይት ረጋሳ(ዶ/ር) በበኩላቸው የኢጋድ አባል ሀገራት ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የግብርና ስራ ለመስራት እያደረጉ ያለውን ጥረት የበለጠ ውጤታማ ለማድረግ ድጋፍ እየተደረገ ነው ብለዋል።

ፕሮግራሙ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የገበያ ትስስር በመፍጠር፣ የግብርና ፖሊሲዎች አሰሪ እንዲሆኑ እንዲሁም የተደራጀ የመረጃ ሥርዓት አያያዝ ላይ የቴክኒክ ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል።

ግብርናን ማዘመንና በቴክኖሎጂ የማገዙ ስራ የበለጠ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል።

በቀጣናው የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ችግሮች እያጋጠሙ መሆኑን ጠቅሰው በተለይም ግብርናው በአየር ንብረት ለውጥ አሉታዊ ተጽዕኖ የሚያርፍበት መሆኑን ጠቅሰዋል።

እንደ ዶክተር ሰናይት ገለጻ የቀጣናው ሀገራት ለአየር ንብረት ለውጥ ያላቸው ድርሻ አነስተኛ ቢሆንም ዋነኛ የችግሩ ገፈት ቀማሽ ሆነዋል።

ይህንን ችግር ለመቋቋም ኢትዮጵያ የጀመረችው የአረንጓዴ አሻራ መርኃ ግብር ለሌሎች ምሳሌ እንደሚሆን ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ የግብርና ኢንቨስትመንትን የበለጠ ለማሳደግ የጀመረቻቸው ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ በመድረኩ ተነስቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026