የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ኢትዮጵያ በግብርና ልማት ለሌሎች ሀገራት ተምሳሌት የሚሆኑ ሥራዎችን እያከናወነች ነው

Apr 22, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 13/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጰያ በግብርና ልማት ለሌሎች ሀገራት ተምሳሌት የሚሆኑ ሥራዎችን እያከናወነች መሆኑ ተገልጿል።

የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎችን አፈጻጸም በተመለከተ ባለድርሻ አካላት ግምገማ አድርገዋል።

የምስራቅ አፍሪካ የልማት በየነ መንግስታት ባለስልጣን(ኢጋድ) አባል ሀገራት የግብርና ልማት አፈጻጸምን በተመለከተ የአፍሪካ የግብርና ልማት ፕሮግራም በየሁለት ዓመቱ ይገመግማል።

ሀገራቱ ለፕሮግራሙ ሪፖርት ከማድረጋቸው በፊት ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ የውይይት መድረክ በማዘጋጀት የየሀገራቸውን አፈጻጸም ይገመግማሉ።

በዚህ መሰረት ኢትዮጵያም የግብርና ልማት ስራዎቿን አፈጻጸም ገምግማለች።

በግብርና ሚኒስቴር የሚኒስትሩ አማካሪ አቶ ዜና ሃብተወልድ እንደሚሉት፣ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የግብርና ልማት ፕሮግራም የተሻለ አፈፃፀም አላት።

ፕሮግራሙ ያስቀመጣቸው መስፈርቶችን በልማት ዕቅዷ በማካተት ተግባራዊ ማድረጓ ለውጤቱ መገኘት ትልቅ ድርሻ ማበርከቱን ጠቅሰዋል።

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት፣ በአረንጓዴ አሻራ፣ በሌማት ትሩፋትና በሌሎች የግብርና ልማት ስራዎች እያስመዘገበችው ያለው ስኬት ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ምሳሌ የሚሆን ነው ብለዋል።

በኢጋድ የምግብ ሥርዓት ፕሮግራም አስተባባሪ ሰናይት ረጋሳ(ዶ/ር) በበኩላቸው የኢጋድ አባል ሀገራት ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የግብርና ስራ ለመስራት እያደረጉ ያለውን ጥረት የበለጠ ውጤታማ ለማድረግ ድጋፍ እየተደረገ ነው ብለዋል።

ፕሮግራሙ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የገበያ ትስስር በመፍጠር፣ የግብርና ፖሊሲዎች አሰሪ እንዲሆኑ እንዲሁም የተደራጀ የመረጃ ሥርዓት አያያዝ ላይ የቴክኒክ ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል።

ግብርናን ማዘመንና በቴክኖሎጂ የማገዙ ስራ የበለጠ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል።

በቀጣናው የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ችግሮች እያጋጠሙ መሆኑን ጠቅሰው በተለይም ግብርናው በአየር ንብረት ለውጥ አሉታዊ ተጽዕኖ የሚያርፍበት መሆኑን ጠቅሰዋል።

እንደ ዶክተር ሰናይት ገለጻ የቀጣናው ሀገራት ለአየር ንብረት ለውጥ ያላቸው ድርሻ አነስተኛ ቢሆንም ዋነኛ የችግሩ ገፈት ቀማሽ ሆነዋል።

ይህንን ችግር ለመቋቋም ኢትዮጵያ የጀመረችው የአረንጓዴ አሻራ መርኃ ግብር ለሌሎች ምሳሌ እንደሚሆን ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ የግብርና ኢንቨስትመንትን የበለጠ ለማሳደግ የጀመረቻቸው ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ በመድረኩ ተነስቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026