
ነገሌ ቦረና፤ሚያዝያ 28/2017(ኢዜአ )፦በምስራቅ ቦረና ዞን በዘንድሮው የበልግ አዝመራ ከ167 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ፡፡
በጽህፈት ቤቱ የሰብል ልማት ባለሙያ አቶ ቦነያ ሁቃ በዞኑ በየዓመቱ ከመጋቢት 15 እስከ ሚያዝያ መጨረሻ የበልግ ወቅት እንደሆነ ገልጸው፤ በዘንድሮ የበልግ እርሻ 158 ሺህ ሄክታር መሬት በዘር ለመሸፈን ታቅዶ ከእቅዱ በላይ መከናወኑን ተናግረዋል።
በዚህም በዞኑ 8 ወረዳዎች 167 ሺህ ሄክታር መሬት በተለያዩ ሰብል ዓይነቶች በዘር መሸፈኑን አስታውቀዋል፡፡
ከዚህ ውስጥ 60 ሺህ ሄክታር የሚሆነው መሬት በስንዴ ምርጥ ዘር የተሸፈነ ሲሆን ከዚህም ከ1 ነጥብ 3 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ መታቀዱን ገልጸዋል፡፡
በዞኑ በበልግ ወቅት በብዘት ከተዘሩት ዋና ዋና የሰብል ዓይነቶች ውስጥ ስንዴ፣ ጤፍ፣ በቆሎ፣ ቦለቄ፤ ሰሊጥ እና ማሾ መሆኑን ጠቅሰው በአጠቃላይ በዘንድሮ የበልግ ወቅት ከ2 ነጥብ 8 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ መታቀዱን ተናግረዋል፡፡
በበልግ አዝመራው ከ147 ሺህ በላይ አርሶ አደሮችና ከፊል አርብቶ አደሮች በልማቱ መሳተፋቸውንም ገልጸዋል፡፡
በጽህፈት ቤቱ የግብዓት አቅርቦትና ስርጭት ባለሙያ አቶ ገመዳ ሀሰን በዞኑ በበልግ አዝመራው 41 ሺህ ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ጥቅም ላይ መዋሉን ጠቁመዋል፡፡
እንዲሁም ከፍተኛ ምርት የሚሰጡ ከ14 ሺህ ኩንታል በላይ የምርጥ ዘር ዓይነቶች ጥቅም ላይ መዋሉንም ተናግረዋል።
ምርታማነትን የሚጨምሩ አዳዲስ የግብርና ሜካናይዜሽን አሰራሮች በመመቻቸታቸው ከዘንድሮ የበልግ አዝመራ ከፍተኛ ምርት ይጠበቃል ብለዋል፡፡
ከአዳዲስ አሰራሮቹ መካከል የእርሻ ትራክተር አቅርቦት፣ የኩታ ገጠም አስተራረስ፣ የግብዓት አቅርቦት እና የታረሰ መሬት ብዛት ዋና ዋናዎቹ እንደሆኑ ጠቅሰዋል፡፡
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026