የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በዞኑ ከ167 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

May 7, 2025

IDOPRESS

ነገሌ ቦረና፤ሚያዝያ 28/2017(ኢዜአ )፦በምስራቅ ቦረና ዞን በዘንድሮው የበልግ አዝመራ ከ167 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ፡፡


በጽህፈት ቤቱ የሰብል ልማት ባለሙያ አቶ ቦነያ ሁቃ በዞኑ በየዓመቱ ከመጋቢት 15 እስከ ሚያዝያ መጨረሻ የበልግ ወቅት እንደሆነ ገልጸው፤ በዘንድሮ የበልግ እርሻ 158 ሺህ ሄክታር መሬት በዘር ለመሸፈን ታቅዶ ከእቅዱ በላይ መከናወኑን ተናግረዋል።


በዚህም በዞኑ 8 ወረዳዎች 167 ሺህ ሄክታር መሬት በተለያዩ ሰብል ዓይነቶች በዘር መሸፈኑን አስታውቀዋል፡፡


ከዚህ ውስጥ 60 ሺህ ሄክታር የሚሆነው መሬት በስንዴ ምርጥ ዘር የተሸፈነ ሲሆን ከዚህም ከ1 ነጥብ 3 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ መታቀዱን ገልጸዋል፡፡


በዞኑ በበልግ ወቅት በብዘት ከተዘሩት ዋና ዋና የሰብል ዓይነቶች ውስጥ ስንዴ፣ ጤፍ፣ በቆሎ፣ ቦለቄ፤ ሰሊጥ እና ማሾ መሆኑን ጠቅሰው በአጠቃላይ በዘንድሮ የበልግ ወቅት ከ2 ነጥብ 8 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ መታቀዱን ተናግረዋል፡፡


በበልግ አዝመራው ከ147 ሺህ በላይ አርሶ አደሮችና ከፊል አርብቶ አደሮች በልማቱ መሳተፋቸውንም ገልጸዋል፡፡


በጽህፈት ቤቱ የግብዓት አቅርቦትና ስርጭት ባለሙያ አቶ ገመዳ ሀሰን በዞኑ በበልግ አዝመራው 41 ሺህ ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ጥቅም ላይ መዋሉን ጠቁመዋል፡፡


እንዲሁም ከፍተኛ ምርት የሚሰጡ ከ14 ሺህ ኩንታል በላይ የምርጥ ዘር ዓይነቶች ጥቅም ላይ መዋሉንም ተናግረዋል።


ምርታማነትን የሚጨምሩ አዳዲስ የግብርና ሜካናይዜሽን አሰራሮች በመመቻቸታቸው ከዘንድሮ የበልግ አዝመራ ከፍተኛ ምርት ይጠበቃል ብለዋል፡፡


ከአዳዲስ አሰራሮቹ መካከል የእርሻ ትራክተር አቅርቦት፣ የኩታ ገጠም አስተራረስ፣ የግብዓት አቅርቦት እና የታረሰ መሬት ብዛት ዋና ዋናዎቹ እንደሆኑ ጠቅሰዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026