
ነቀምቴ፤ግንቦት 16/2017(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ወለጋ ዞን በ2017/18 መኸር እርሻ ከ800 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን የዞኑ ግብርና ፅህፈት ቤት ገለጸ።
የፅህፈት ቤቱ ሀላፊ አቶ አስፋው ሀምቢሳ እንዳሉት፥ በመኸር አዝመራ ከሚታረሰው መሬት የተሻለ ምርት ለማግኘት የግብዓት አቅርቦት በስፋት እየተከናወነ ነው።
በዚህም በዞኑ ለመኸር እርሻ የሚውል ከ18 ሺህ ኩንታል በላይ የበቆሎ ምርጥ ዘር በሕብረት ስራ ማህበራት በኩል ለአርሶ አደሩ መቅረቡን ተናግረዋል።
ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግም እስካሁን ከ425 ሺህ ኩንታል በላይ የአፈር መዳበሪያ ለአርሶ አደሩ ማሰራጨት መቻሉን ጠቁመዋል።
ዘንድሮ ከ20 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በሜካናይዝድ መንገድ የሚታረስ ሲሆን የኩታ ገጠም አስተራረስ ዘዴም በስፋት እየተተገበረ መሆኑን ተናግረዋል።
በአጠቃላይ በምርት ዘመኑ 808 ሺህ 200 ሄክታር መሬት በማልማት የተሻለ ምርት ለማግኘት የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026