ነቀምቴ፤ግንቦት 16/2017(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ወለጋ ዞን በ2017/18 መኸር እርሻ ከ800 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን የዞኑ ግብርና ፅህፈት ቤት ገለጸ።
የፅህፈት ቤቱ ሀላፊ አቶ አስፋው ሀምቢሳ እንዳሉት፥ በመኸር አዝመራ ከሚታረሰው መሬት የተሻለ ምርት ለማግኘት የግብዓት አቅርቦት በስፋት እየተከናወነ ነው።
በዚህም በዞኑ ለመኸር እርሻ የሚውል ከ18 ሺህ ኩንታል በላይ የበቆሎ ምርጥ ዘር በሕብረት ስራ ማህበራት በኩል ለአርሶ አደሩ መቅረቡን ተናግረዋል።
ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግም እስካሁን ከ425 ሺህ ኩንታል በላይ የአፈር መዳበሪያ ለአርሶ አደሩ ማሰራጨት መቻሉን ጠቁመዋል።
ዘንድሮ ከ20 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በሜካናይዝድ መንገድ የሚታረስ ሲሆን የኩታ ገጠም አስተራረስ ዘዴም በስፋት እየተተገበረ መሆኑን ተናግረዋል።
በአጠቃላይ በምርት ዘመኑ 808 ሺህ 200 ሄክታር መሬት በማልማት የተሻለ ምርት ለማግኘት የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል።
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...
Feb 12, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...
Feb 8, 2025