የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በዞኑ በዘንድሮው የመኸር እርሻ ከ800 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በመኸር አዝመራ ይለማል

May 26, 2025

IDOPRESS

ነቀምቴ፤ግንቦት 16/2017(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ወለጋ ዞን በ2017/18 መኸር እርሻ ከ800 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን የዞኑ ግብርና ፅህፈት ቤት ገለጸ።


የፅህፈት ቤቱ ሀላፊ አቶ አስፋው ሀምቢሳ እንዳሉት፥ በመኸር አዝመራ ከሚታረሰው መሬት የተሻለ ምርት ለማግኘት የግብዓት አቅርቦት በስፋት እየተከናወነ ነው።


በዚህም በዞኑ ለመኸር እርሻ የሚውል ከ18 ሺህ ኩንታል በላይ የበቆሎ ምርጥ ዘር በሕብረት ስራ ማህበራት በኩል ለአርሶ አደሩ መቅረቡን ተናግረዋል።


ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግም እስካሁን ከ425 ሺህ ኩንታል በላይ የአፈር መዳበሪያ ለአርሶ አደሩ ማሰራጨት መቻሉን ጠቁመዋል።


ዘንድሮ ከ20 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በሜካናይዝድ መንገድ የሚታረስ ሲሆን የኩታ ገጠም አስተራረስ ዘዴም በስፋት እየተተገበረ መሆኑን ተናግረዋል።


በአጠቃላይ በምርት ዘመኑ 808 ሺህ 200 ሄክታር መሬት በማልማት የተሻለ ምርት ለማግኘት የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026