የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ የልማት አጀንዳዎች ከብሔራዊ እቅዶች ጋር ተጣጥመው እየተተገበሩ ነው

Jun 20, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሰኔ 11/2017(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ የልማት አጀንዳዎችን ከብሔራዊ እቅዶች ጋር አጣምራ መተግበሯን አጠናክራ እንደምትቀጥል የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዴኤታ ጥሩማር አባተ ገለጹ።

ላላፉት ሦስት ቀናት በአዲስ አበባ ሲካሄድ የቆየው የአፍሪካ የግምገማ ማህበር 25ኛ ዓመት የምስረታ በዓል ተጠናቋል።

የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዴኤታ ጥሩማር አባተ እንደተናገሩት፤ የተካሄደው መርሃ ግብር እንግዶችን በማስተናገድና ኹነቶችን በማካሄድ ስኬታማ ነበር።


የምዘና ስርዓትን ለማጠናከር የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችን ለመስጠት፣ የአገራት ልምድና ተሞክሮ ለመለዋወጥና ትብብርን ለማጠናከር የተያዘውን ግብ ለማሳካት እንደተቻለም አብራርተዋል።

አገራት እንደየነባራዊ ሁኔታቸው የሚከተሉትን የምዘና ስርዓት በመድረኩ ልምዳቸውን ያካፈሉ ሲሆን፤ ኢትዮጵያም ጠንካራ የክትትልና ግምገማ ስርዓትን ለመዘርጋት ያከናወነቻቸውን ተግባራት ማቅረቧን ገልጸዋል።

አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ የልማት እቅዶችን ከብሔራዊ እቅዶቿ ጋር በማጣመርና የትግበራ ሂደታቸውን ሪፖርት፣ ክትትልና ግምገማ በማድረግ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።


ኢትዮጵያ እየተገበረች የምትገኘው የ10 ዓመት የልማት እቅድ እና አጀንዳ 2063 የዘላቂ ልማት ግቦችን አጣምሮ የያዘ መሆኑን በማስታወስ፤ በቀጣይም ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።

በአገር ነባራዊ ሁኔታዎች ላይ የተመሰረተ የፖሊሲ ውሳኔና ሪፎርም ማህበረሰብን ተጠቃሚ ማድረጉን ለማወቅ ጠንካራ የክትትልና ምዘና ስርዓት ወሳኝ በመሆኑ በትኩረት እየተሰራ ይገኛልም ነው ያሉት።

የአፍሪካ ህብረት ሊቀ መንበር ተወካይ አምባሳደር ሞሃመድ ኢልአሚኒ በበኩላቸው፤ በአህጉሪቷ በመረጃ ላይ የተመሰረተ የፖሊሲ ውሳኔ በመስጠት እንዲሁም አፈጻጸሙን ክትትል በማድረግ ለማህበረሰብ ተጠቃሚነት መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።


የአፍሪካ የግምገማ ማህበር በአጀንዳ 2063 ትግበራ በትብብር መስራቱን አጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀው፤ አገራት ለአቅም ግንባታ ትኩረት እንዲሰጡ አሳስበዋል።

የአፍሪካ ግምገማ ማህበር ፕሬዝዳንት ሚቼ ኦዲራጎ በበኩላቸው፤ ባለፉት ሶስት ቀናት በአፍሪካ በመረጃ ላይ የተመሰረተ የፖሊሲ ውሳኔ መስጠት የሚያስችል የግምገማ ስርዓትንና ትብብርን የሚያጠናክሩ ኹነቶች መካሄዳቸውን ገልጸዋል።


አንድነቷ የተጠናከረና በምጣኔ ሃብት የበለጸገች አፍሪካን እውን ለማድረግ በዘላቂ ልማት ግቦችና አጀንዳ 2063 ለሚተገበሩ የልማት መርሃ ግብሮች ማህበሩ ከአገራት ጋር በትብብር የሚሰራውን ስራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።

በአፍሪካ የግምገማ ማህበር 25ኛ ዓመት የምስረታ በዓል ላይ ከአፍሪካ እና ሌሎች የዓለም አገራት የተውጣጡ ባለሙያዎች፣ ምሁራን፣ ፖሊሲ አውጭዎችና ከ300 በላይ እንግዶች ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026