
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 12/2017(ኢዜአ)፦ በወንጀል ድርጊት የተገኘ ንብረት ወይም ገንዘብ ህጋዊ አስመስሎ ማቅረብ እና ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳትን ለመቆጣጠርና ለመከላከል የተሻሻለው አዋጅ ሽብርተኝነትንና ወንጀልን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የሚያስችል እንዲሁም ከዓለም አቀፍ ህጎች ጋር የተጣጣመ መሆኑን የፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት አስታወቀ።
በወንጀል ድርጊት የተገኘን ንብረት ወይም ገንዘብ ህጋዊ አስመስሎ ማቅረብ እና ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳትን ለመቆጣጠርና ለመከላከል የወጣውን አዋጅ ቁጥር 780/2005ን ለማሻሻል የወጣውን አዋጅ ቁጥር 1387/2017 ሰኔ 10 ቀን 2017 ዓ.ም በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መጽደቁ ይታወቃል።
በተሻሻለው አዋጅ ዙሪያ ለህብረተሰቡ ተጨማሪ መረጃን ተደራሽ ለማድረግም የፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሙሉቀን አማረ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል።
በመግለጫቸውም የተሻሻለው አዋጅ ቁጥር 1387/2017 ከነባር አዋጁ 780/2005 በ58 አንቀጾች 14ቱ ላይ ማሻሻያ አድርጓል ብለዋል።
አዋጁ ሽብርተኝነትንና ወንጀልን መከላከልና መቆጣጠር የሚያስችል እንዲሁም ከዓለም አቀፍ ህጎች ጋር የተጣጣመ መሆኑን ተናግረዋል።
የማሻሻያ አዋጁ በወንጀል ተግባር የተገኘ ገንዘብን ወይም ንብረትን ሕጋዊ አስመስሎ ማቅረብ እና ሽብርተኝነትን በገንዘብ የመርዳት ወንጀል ድርጊትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር በሚደረገው ዓለም አቀፍ ጥረት ላይ ኢትዮጵያ ድርሻዋን በአግባቡ እንድትወጣ ያስችላል ብለዋል።
አዋጁ አመንጪ የሚባሉ 21 ወንጀሎችን በአባሪነት ያስቀመጠ ብሎም ለትርጉም ተጋላጭ የነበሩ ጉዳዮችን በግልጽ የሚየስቀምጥ መሆኑን ጠቁመው፤ ይህም ተገቢ ምርመራ ለማካሄድ እንደሚጠቅም ገልጸዋል።
በወንጀል ድርጊት የቅጣት አለመመጣጠን መልክ ማስያዝ የሚያስችል ጭምር መሆኑንም ተናግረዋል።
በሽፋን ስር ለሚደረጉ የምርመራ ሂደቶች ወይንም ልዩ የምርመራ ሂደቶች በፍርድ ቤት ትዕዛዝ ብቻ የሚከናወን መሆኑን ማስቀመጡን ገልጸዋል።
ይህም ፍርድ ቤቱ በመደበኛ የምርመራ ዘዴ ማስረጃ ማግኘት አዳጋች መሆኑን አምኖ በሰጠው ፈቃድና ትዕዛዝ መሠረት የሚከናወን መሆኑንም ጠቁመዋል።
ይህ የምርመራ ዘዴ በፍርድ ቤት ትዕዛዝ የሚደረግ መረጃን ለማግኘት በጥብቅ ዲሲፕሊን እና በፍርድ ቤት ቁጥጥር ስር የሚከናወን መሆኑንም ገልጸዋል።
በአጠቃላይም የተሻሻለው አዋጅ የሀገርን ደህንነትና የህዝብን ጥቅም የሚያስጠብቅ መሆኑን ነው አቶ ሙሉቀን አማረ የጠቆሙት።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026