
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 12/2017(ኢዜአ)፦ በወንጀል ድርጊት የተገኘ ንብረት ወይም ገንዘብ ህጋዊ አስመስሎ ማቅረብ እና ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳትን ለመቆጣጠርና ለመከላከል የተሻሻለው አዋጅ ሽብርተኝነትንና ወንጀልን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የሚያስችል እንዲሁም ከዓለም አቀፍ ህጎች ጋር የተጣጣመ መሆኑን የፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት አስታወቀ።
በወንጀል ድርጊት የተገኘን ንብረት ወይም ገንዘብ ህጋዊ አስመስሎ ማቅረብ እና ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳትን ለመቆጣጠርና ለመከላከል የወጣውን አዋጅ ቁጥር 780/2005ን ለማሻሻል የወጣውን አዋጅ ቁጥር 1387/2017 ሰኔ 10 ቀን 2017 ዓ.ም በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መጽደቁ ይታወቃል።
በተሻሻለው አዋጅ ዙሪያ ለህብረተሰቡ ተጨማሪ መረጃን ተደራሽ ለማድረግም የፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሙሉቀን አማረ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል።
በመግለጫቸውም የተሻሻለው አዋጅ ቁጥር 1387/2017 ከነባር አዋጁ 780/2005 በ58 አንቀጾች 14ቱ ላይ ማሻሻያ አድርጓል ብለዋል።
አዋጁ ሽብርተኝነትንና ወንጀልን መከላከልና መቆጣጠር የሚያስችል እንዲሁም ከዓለም አቀፍ ህጎች ጋር የተጣጣመ መሆኑን ተናግረዋል።
የማሻሻያ አዋጁ በወንጀል ተግባር የተገኘ ገንዘብን ወይም ንብረትን ሕጋዊ አስመስሎ ማቅረብ እና ሽብርተኝነትን በገንዘብ የመርዳት ወንጀል ድርጊትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር በሚደረገው ዓለም አቀፍ ጥረት ላይ ኢትዮጵያ ድርሻዋን በአግባቡ እንድትወጣ ያስችላል ብለዋል።
አዋጁ አመንጪ የሚባሉ 21 ወንጀሎችን በአባሪነት ያስቀመጠ ብሎም ለትርጉም ተጋላጭ የነበሩ ጉዳዮችን በግልጽ የሚየስቀምጥ መሆኑን ጠቁመው፤ ይህም ተገቢ ምርመራ ለማካሄድ እንደሚጠቅም ገልጸዋል።
በወንጀል ድርጊት የቅጣት አለመመጣጠን መልክ ማስያዝ የሚያስችል ጭምር መሆኑንም ተናግረዋል።
በሽፋን ስር ለሚደረጉ የምርመራ ሂደቶች ወይንም ልዩ የምርመራ ሂደቶች በፍርድ ቤት ትዕዛዝ ብቻ የሚከናወን መሆኑን ማስቀመጡን ገልጸዋል።
ይህም ፍርድ ቤቱ በመደበኛ የምርመራ ዘዴ ማስረጃ ማግኘት አዳጋች መሆኑን አምኖ በሰጠው ፈቃድና ትዕዛዝ መሠረት የሚከናወን መሆኑንም ጠቁመዋል።
ይህ የምርመራ ዘዴ በፍርድ ቤት ትዕዛዝ የሚደረግ መረጃን ለማግኘት በጥብቅ ዲሲፕሊን እና በፍርድ ቤት ቁጥጥር ስር የሚከናወን መሆኑንም ገልጸዋል።
በአጠቃላይም የተሻሻለው አዋጅ የሀገርን ደህንነትና የህዝብን ጥቅም የሚያስጠብቅ መሆኑን ነው አቶ ሙሉቀን አማረ የጠቆሙት።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026