
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 13/2017(ኢዜአ)፦ መንግስት በየአካባቢው ያሉ ሀብቶችን በማልማት ያከናወናቸው ተግባራት ሀገራዊ ዕድገትን ማረጋገጥ እንደሚቻል ያመላከተ ነው ሲሉ የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች ገለጹ።
በአርባ ምንጭ ከተማና አካባቢው እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎች ከተማዋን የኮንፍረንስ ቱሪዝም ማዕከል የሚያደርጋት መሆኑን ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮቹ አክለው ተናግረዋል።
የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች በአርባ ምንጭ ከተማ የሚገኙ የተለያዩ የልማት ስራዎችን ጎብኝተዋል።

በጉብኝታቸውም የገበታ ለትውልድ አካል የሆነውንና በግንባታ ሥራ ላይ የሚገኘውን የአርባ ምንጭ ኮንፍረንስ ሪዞርት ፕሮጀክት፣ የኮሪደር ልማት፣ የአርባምንጭ ዓለም አቀፍ ስታዲየም፣ የአዞ ራንች፣ አርባምንጮችንና ሌሎች የልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል።
አስተያየታቸውን ለኢዜአ ከሰጡት መካከል የወሎ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ፕሬዚዳንት ነፃነት ጣሰው እንዳሉት፤ በአርባ ምንጭ ከተማና አካባቢው የተከናወኑ የልማት ተግባራት ሀገር እምቅ ተፈጥሯዊ ሀብቷን በመጠቀም የልማት ጉዞ ላይ እንደምትገኝ ያመላክታል።
የልማት ሥራዎቹ እንደሀገር ለተጀመሩ ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ ዕድገት ተጨማሪ አቅም የሚሆኑ ናቸው ብለዋል።

በተለይ በገበታ ለትውልድ እየተገነባ ያለው የአርባምንጭ ኮንፍረንስ ሪዞርት ከተማዋን የኮንፍረንስ ቱሪዝም ማዕከል ያደርጋታል ብለው እንደሚያምኑም ገልጸዋል።
ፓርቲያቸው እንደሀገር በሚከናወኑ የልማት ሥራዎች ከመንግሥት ጋር በትብብር እንደሚሰራም አረጋግጠዋል።
የትንሳኤ ሰብዓ እንደርታ ፓርቲ ሊቀ መንበር ከበደ አሰፋ በበኩላቸው፤ መንግስት በየአካባቢው መጪውን ትውልድ ታሳቢ አድርጎ እየሰራቸው ያሉ ሥራዎች አስደናቂ ናቸው ብለዋል።
እነዚህ ሥራዎች የተሻለች ሀገርን ለመጪው ትውልድ ማስተላለፍ እንደሚቻል የሚያረጋግጥ እንደሆነም ተናግረዋል።
የጉሙዝ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ ሊቀ መንበር ግራኝ ጉደታ በበኩላቸው፤ መንግስት የሀገርን ሁለንተናዊ እድገት ለማረጋገጥ እያከናወነ ያለው የልማት ሥራዎች አበረታች ናቸው።

የሀገርንና የዜጎችን ተጠቃሚነት በሚያረጋግጡ ጉዳዮች ዙሪያ በጋራ ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውንም ጨምረው ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ዲሞክራቲክ ህብረት የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ ሳሙኤል ብርሃኑ እንደተናገሩት፤ የተመለከቷቸው ስራዎች ሀገራዊ ልማትን የሚያመላክቱ ናቸው።
የቅማንት ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ ምክትል ሊቀ መንበር ተገኑ ደረጀ በበኩላቸው፤ የልማት ሥራዎች ሁለንተናዊ ልማት የሚያረጋግጡ በመሆናቸው ከመንግሥት ጋር በትብብር እንሰራለን ብለዋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026