የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

መንግስት በየአካባቢው ያሉ ሀብቶችን በማልማት ያከናወናቸው ተግባራት ሀገራዊ ዕድገትን ማረጋገጥ እንደሚቻል አመለካች ነው

Jun 23, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 13/2017(ኢዜአ)፦ መንግስት በየአካባቢው ያሉ ሀብቶችን በማልማት ያከናወናቸው ተግባራት ሀገራዊ ዕድገትን ማረጋገጥ እንደሚቻል ያመላከተ ነው ሲሉ የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች ገለጹ።

በአርባ ምንጭ ከተማና አካባቢው እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎች ከተማዋን የኮንፍረንስ ቱሪዝም ማዕከል የሚያደርጋት መሆኑን ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮቹ አክለው ተናግረዋል።

የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች በአርባ ምንጭ ከተማ የሚገኙ የተለያዩ የልማት ስራዎችን ጎብኝተዋል።


በጉብኝታቸውም የገበታ ለትውልድ አካል የሆነውንና በግንባታ ሥራ ላይ የሚገኘውን የአርባ ምንጭ ኮንፍረንስ ሪዞርት ፕሮጀክት፣ የኮሪደር ልማት፣ የአርባምንጭ ዓለም አቀፍ ስታዲየም፣ የአዞ ራንች፣ አርባምንጮችንና ሌሎች የልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል።

አስተያየታቸውን ለኢዜአ ከሰጡት መካከል የወሎ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ፕሬዚዳንት ነፃነት ጣሰው እንዳሉት፤ በአርባ ምንጭ ከተማና አካባቢው የተከናወኑ የልማት ተግባራት ሀገር እምቅ ተፈጥሯዊ ሀብቷን በመጠቀም የልማት ጉዞ ላይ እንደምትገኝ ያመላክታል።

የልማት ሥራዎቹ እንደሀገር ለተጀመሩ ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ ዕድገት ተጨማሪ አቅም የሚሆኑ ናቸው ብለዋል።


በተለይ በገበታ ለትውልድ እየተገነባ ያለው የአርባምንጭ ኮንፍረንስ ሪዞርት ከተማዋን የኮንፍረንስ ቱሪዝም ማዕከል ያደርጋታል ብለው እንደሚያምኑም ገልጸዋል።

ፓርቲያቸው እንደሀገር በሚከናወኑ የልማት ሥራዎች ከመንግሥት ጋር በትብብር እንደሚሰራም አረጋግጠዋል።

የትንሳኤ ሰብዓ እንደርታ ፓርቲ ሊቀ መንበር ከበደ አሰፋ በበኩላቸው፤ መንግስት በየአካባቢው መጪውን ትውልድ ታሳቢ አድርጎ እየሰራቸው ያሉ ሥራዎች አስደናቂ ናቸው ብለዋል።

እነዚህ ሥራዎች የተሻለች ሀገርን ለመጪው ትውልድ ማስተላለፍ እንደሚቻል የሚያረጋግጥ እንደሆነም ተናግረዋል።

የጉሙዝ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ ሊቀ መንበር ግራኝ ጉደታ በበኩላቸው፤ መንግስት የሀገርን ሁለንተናዊ እድገት ለማረጋገጥ እያከናወነ ያለው የልማት ሥራዎች አበረታች ናቸው።


የሀገርንና የዜጎችን ተጠቃሚነት በሚያረጋግጡ ጉዳዮች ዙሪያ በጋራ ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውንም ጨምረው ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ዲሞክራቲክ ህብረት የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ ሳሙኤል ብርሃኑ እንደተናገሩት፤ የተመለከቷቸው ስራዎች ሀገራዊ ልማትን የሚያመላክቱ ናቸው።

የቅማንት ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ ምክትል ሊቀ መንበር ተገኑ ደረጀ በበኩላቸው፤ የልማት ሥራዎች ሁለንተናዊ ልማት የሚያረጋግጡ በመሆናቸው ከመንግሥት ጋር በትብብር እንሰራለን ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026