አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2017(ኢዜአ)፦ መንግስት ለህክምናው ዘርፍ 130 ቢሊየን ብር የሚጠጋ ሀብት እየበጀተ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከመላው ኢትዮጵያ ከተውጣጡ የጤና ባለሞያዎች ጋር ተወያይተዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ መንግስት የጤናውን ዘርፍ ውጤታማ ለማድረግ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ አብራርተዋል፡፡
በዚህም ባለፉት አመታት ወደ ለጤና ዘርፉ እየመደበ ያለውን በጀት እያሳደገ ይገኛል ብለዋል፡፡
ከጥቂት አመታት በፊት በቀጥታ ለጤናው ዘርፍ ይመደብ የነበረው ሀብት 70 ቢሊየን ብር ገደማ እንደነበር አስታውሰው፤ በአሁኑ ወቅት መንግስት 130 ቢሊየን የሚጠጋ ሀብት መመደቡን አስታውቀዋል፡፡
ከዚህም በተጨማሪ ባለፈው ዓመት መንግስት 9 ቢሊዮን ብር ለመድሃኒት ግዥ ድጎማ ማድርጉን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
መንግስት ለህክምናው ዘርፍ የሚያወጣው ወጪ ከየትኛውም ጎረቤት ሀገራት እንደሚበልጥም ተናግረዋል።
በጤናው ዘርፍ መንግስት ለግንባታ የሚያወጣውን ወጪ የትኛውም ጎረቤት ሀገር እንደማያወጣ ጨምረው አንስተዋል።
ምንም እንኳን ለጤናው ዘርፍ የሚበጀተው በጀት እያደገ ቢሆንም ካለው ፍላጎት አንጻር ገና መሆኑን ጠቅሰዋል።
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...
Feb 12, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...
Feb 8, 2025