
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2017(ኢዜአ)፦ መንግስት ለህክምናው ዘርፍ 130 ቢሊየን ብር የሚጠጋ ሀብት እየበጀተ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከመላው ኢትዮጵያ ከተውጣጡ የጤና ባለሞያዎች ጋር ተወያይተዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ መንግስት የጤናውን ዘርፍ ውጤታማ ለማድረግ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ አብራርተዋል፡፡
በዚህም ባለፉት አመታት ወደ ለጤና ዘርፉ እየመደበ ያለውን በጀት እያሳደገ ይገኛል ብለዋል፡፡

ከጥቂት አመታት በፊት በቀጥታ ለጤናው ዘርፍ ይመደብ የነበረው ሀብት 70 ቢሊየን ብር ገደማ እንደነበር አስታውሰው፤ በአሁኑ ወቅት መንግስት 130 ቢሊየን የሚጠጋ ሀብት መመደቡን አስታውቀዋል፡፡
ከዚህም በተጨማሪ ባለፈው ዓመት መንግስት 9 ቢሊዮን ብር ለመድሃኒት ግዥ ድጎማ ማድርጉን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
መንግስት ለህክምናው ዘርፍ የሚያወጣው ወጪ ከየትኛውም ጎረቤት ሀገራት እንደሚበልጥም ተናግረዋል።
በጤናው ዘርፍ መንግስት ለግንባታ የሚያወጣውን ወጪ የትኛውም ጎረቤት ሀገር እንደማያወጣ ጨምረው አንስተዋል።
ምንም እንኳን ለጤናው ዘርፍ የሚበጀተው በጀት እያደገ ቢሆንም ካለው ፍላጎት አንጻር ገና መሆኑን ጠቅሰዋል።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026